0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMአቶ ታዬ ደንደአ የዋስ መብት ተከለከሉየፌዴራል ጠቅላይ ፍርድ ቤት የቀድሞው የሰላም ሚንስትር ድኤታ አቶ ታዬ ደንደአ ያቀረቡትን የዋስትና መብት ጥያቄ ውድቅ አደረገ። አቃቤ ሕግ ካቀረበባቸዉ ክሶች ሁለቱ ውድቅ የተደረገላቸው አቶ ታዬ፣ በዛሬው ዕለት ስድስት ኪሎ ከሚገኘው የፌደራሉ ጠቅላይ ፍርድ ቤት ፊት ቀርበው የዋስትና መብታቸው እንዲከበር ያቀረቡትን አቤቱታ ቀደም ሲል የልደታ ከፍተኛ ፍርድ ቤት ያሳለፈውን የፍርድ ውሳኔ በማፅናት ነው ጥያቄያቸውን ውድቅ ያደረገው።0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየቻይና-አፍሪካ ትብብር ጉባኤ ተጀመረኢትዮጵያን ጨምሮ ከ50 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የታደሙበት የቻይና-አፍሪካ የትብብር ጉባዔ ዛሬ በቤጂንግ ተከፍቷል። ለሦስት ቀናት በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ላይ፣ እስከ አውሮፓውያኑ 2027 በሚኖረው የቻይና እና አፍሪካ ግንኙነት የትብብር ሰነዶች ላይ ውይይት ተደርጎ ስምምነት እንደሚፈረም ይጠበቃል፡፡ በጉባኤው ለመሳተፍ ቤጂንግ ከገቡ የአፍሪካ መሪዎች አንዱ የሆኑት፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ቻይና አበርክታለች ያሉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMሂዩማን ራይትስ ዋች “ሊባኖስና ቆጵሮስ ፍልሰተኞችን ወደ ሶሪያ መልሰው እያባረሩ ነው” አለዓለም አቀፉ የሰብአዊ መብቶቶች ድርጅት ሂዩማን ራይትስ ዎች የሊባኖስ ጦር እና በአቅራቢያው ቆጵሮስ የሚገኙ ባለሥልጣናት ፍልስተኞች ወደ አውሮፓ እንዳይደርሱ በማድረግ በጦርነት ወደ ታመሰችው ሶሪያ መልሰው በማባረር በጋራ እየሰሩ ነው ሲል ከሰሰ፡፡ የሊባኖስ ጦር በጀልባ ለመውጣት የሚሞክሩትን ሶሪያውያን ስደተኞችን “ ይዞ በመመለስ ወዲያውኑ ወደ ሶሪያ እንዳሚያባርራቸው” የመብት ተሟጋቹ ድርጅት ባወጣው መግለጫ አስታውቋል። የባህር ዳርቻ ጠባቂዎችን ጨምሮ የቆጵሮስ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMዩናይትድ ስቴትስ ሩሲያን ፕሬዝዳንታዊ ምርጫውን ኢላማ ባደረጉ የሀሰተኛ መረጃ ዘመቻ በማካሄድ ልትወነጅል ተዘጋጅታለችየባይደን አስተዳደር ሩሲያን ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ላይ ባነጣጠሩ የሃሰት መረጃ ቅስቀሳዎች ለመክሰስ በዝግጅት ላይ መሆኑን ስለጉዳዩ ቅርበት ያላቸውን ሰዎች ተናገሩ፡፡ ከመግለጫው በፊት በይፋ መናገር ያልተፈቀደላቸው በመሆኑ ስማቸው ያልተገለጸ ሰዎችን ጠቅሶ አሶሴይትድ ፕሬስ እንደዘገበው የዩናይትድ ስቴትስ ጠቅላይ አቃቤ ህግ ሜሪክ ጋርላንድ ዛሬ ረቡዕ ስለጉዳዩ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ ይጠበቃል፡፡ የስለላ ተቋማት ቀደም ሲል ሩሲያ በምርጫው ውስጥ ጣልቃ ለመግባት...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኩሌባ የሥራ መልቀቂያ አቀረቡየዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ዛሬ ረቡዕ የሥራ መልቀቂያ አቀረቡ፡፡ በዓለም አቀፍ ደረጃ ዩክሬንን በመወከል ታዋቂ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የ43 ዓመቱ ኩሌባ ከሥልጣን ለመልቀቅ የፈለጉበትን ምክንያት አላቀረቡም፡፡ የመልቀቂያው ጥያቄቸውን ምክር ቤቱ በሚቀጥለው ስብሰባ እንደሚነጋገርበት የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ሩስላን ስቴፋንቸክ በፌስ ቡክ ገጻቸው ተናግረዋል፡፡ ኩሌባ መልቀቂያውን ያቀረቡት ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜለንስኪ ለጦርነቱ ቀጣይ ወሳኝ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMአዲስ ተጨማሪ የሽያጭ ግብር በማሕበረሰቡ ላይ ምን አይነት ጫና ያሳደር ይሆን?የገንዘብ ሚንስቴር ባለፉት 22 ዓመታት ከተጨማሪ እሴት የሽያጭ ግብር ነፃ ተደርገው ቆይተዋል ባላቸው የኤሌክትሪክ ፣ የውሃ አቅርቦት እና የትራንስፖርት ዘርፍ ላይ ተጨማሪ እሴት ግብር ተግባራዊ ማድረግ እንደሚጀምር ነሐሴ 23, 2016ዓ.ም በማሕበራዊ የትስስር ገጹ ባወጣው የጽሁፍ መግለጫ አስታውቋል፡፡ ይህ ተጨማሪ እሴት ታክስ ቋሚና አነስተኛ ገቢ ያለው ማህበረሰብ ላይ ጫና የሚፈጥር ነው ሲሉ የአሜሪካ ድምጽ ያነጋገራቸው የምጣኔ ሃብት ባለሙያ እና...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMኢትዮጵያ ፍላጎቷን ለማሟላት ቢያንስ አስር ወደቦች ያስፈልጋታል – የጅቡቲ ሚኒስትርበኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል የፈጠረውን አለመግባባት ለመፍታት፣ ጅቡቲ ከኢትዮጵያ ድንበር በ100 ኪሎሜትር ርቀት ላይ የሚገኘውን ታጁራ ወደብ ኢትዮጵያ እንድትጠቀምበት ማቅረቧን የጅቡቲ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ማህሙድ አሉ ዩሱፍ ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል። ሆኖም ይህ አማራጭ ኢትዮጵያ የባሕር ኃይል ለመገንባት ያላትን ፍላጎት እንደማያካትት ሚንስትሩ አመልክተዋል።0 Comments 0 Shares