•  ኤምቲኤን” እና “ቮዳፎን” ከቴሌ ድርሻ ለመግዛት አቅደዋል    የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል ይዞታ የማዛወሩ ሂደት በጥናት   በጥንቃቄና በጥብቅ ዲሲፒሊን እንደሚፈፀም ገዥው ፓርቲ ባወጣው የአፈፃፀም ዝርዝር ያስታወቀ ሲሆን የደቡብ አፍሪካዎቹ “ቮዳፎን” እና “ኤምቲ ኤን” “ኩባንያዎች በበኩላቸው፤ ከኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ከወዲሁ መግለፃቸው ታውቋል፡፡የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሜ ኮሚቴ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወደ ግል ይዞታነት የሚዛወሩበትን ዝርዝር በተመለከተ ባወጣው መመሪያ፤ የባቡር፣ የስኳር ልማት፣ የኢንዱስትሪ ፓርክ፣ የሆቴልና የማኑፋክቸሪንግ ድርጅቶች ድርሻ ሊሸጥ የሚችለው ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ነው ብሏል፡፡ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫዎች እና የባህር ትራንስፖርት ሎጅስቲክ ድርጅት ለሃገር ውስጥና ለውጪ ባለሃብት ገበያ የቀረቡ መሆኑን የጠቆመው ገዥው ፓርቲ፤ በእነዚሀ ኩባንያዎች ውስጥ የመንግስት አክሲዮን ድርሻ አብላጫ እንደሚሆን ጠቁሟል፡፡ከላይ በተጠቀሱት ሜጋ ፕሮጀክቶች እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የባለሃብቱ አቅም እየተጠናከረ መሄዱን በማጤን ሙሉ ለሙሉ መንግስት የሚወጣበት ስትራቴጂ መቀመጡም ተጠቁሟል፡፡ ገዥው ፓርቲ እነዚህን የልማት ድርጅቶች ወደ ግል ለማዞር ሶስት አበይት ሁኔታዎችን ታሣቢ በማድረግ መወሠኑንም አስታውቋል፡፡ የመጀመሪያ የውጪ ንግድን ለማሣደግ አጋዥ ይሆናል ከሚል እሣቤ ሲሆን ሁለተኛው ታሣቢ ዜጎችን አካታች የሆነ ሃገራዊ እድገት ማስመዝገብ መሆኑን ይገልፃል፡፡ ሦስተኛው ደግሞ የልማት ድርጅቶች በምርታማነት፣ በአገልግሎት አሠጣጥ ጥራታቸውና አቅማቸው ውጤታማ ሆነው ወደ አለማቀፋዊ ተወዳዳሪነት እንዲያድጉ አጋዥ ይሆናል ከሚል እሳቤ መሆኑን ፓርቲው አስታውቋል፡፡ በዚህ የአክሲዮን ሽያጭ የውጭ ምንዛሬና የካፒታል ገቢ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ የመንግስት ውሣኔን ተከትሎ በበርካታ የአፍሪካ ሃገራት በቴሌኮም ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙት “ኤምቲ ኤን” እና “ቮዳፎን” የተሠኙት ግዙፍ የደቡብ አፍሪካ የግል የቴሌኮም ኩባንያዎች፣ ከቴሌ አክሲዮን ለመግዛት ፍላጎት እንዳላቸውና በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እንደሚነጋገሩ አስታወቋል፡፡
     ኤምቲኤን” እና “ቮዳፎን” ከቴሌ ድርሻ ለመግዛት አቅደዋል    የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል ይዞታ የማዛወሩ ሂደት በጥናት   በጥንቃቄና በጥብቅ ዲሲፒሊን እንደሚፈፀም ገዥው ፓርቲ ባወጣው የአፈፃፀም ዝርዝር ያስታወቀ ሲሆን የደቡብ አፍሪካዎቹ “ቮዳፎን” እና “ኤምቲ ኤን” “ኩባንያዎች በበኩላቸው፤ ከኢትዮ ቴሌኮም የአክሲዮን ድርሻ ለመግዛት ፍላጎት እንዳላቸው ከወዲሁ መግለፃቸው ታውቋል፡፡የኢህአዴግ ስራ አስፈፃሜ ኮሚቴ የመንግስት የልማት ድርጅቶች ወደ ግል ይዞታነት የሚዛወሩበትን ዝርዝር በተመለከተ ባወጣው መመሪያ፤ የባቡር፣ የስኳር ልማት፣ የኢንዱስትሪ ፓርክ፣ የሆቴልና የማኑፋክቸሪንግ ድርጅቶች ድርሻ ሊሸጥ የሚችለው ለሃገር ውስጥ ባለሃብቶች ብቻ ነው ብሏል፡፡ኢትዮ ቴሌኮም፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ፣ የኤሌክትሪክ ሃይል ማመንጫዎች እና የባህር ትራንስፖርት ሎጅስቲክ ድርጅት ለሃገር ውስጥና ለውጪ ባለሃብት ገበያ የቀረቡ መሆኑን የጠቆመው ገዥው ፓርቲ፤ በእነዚሀ ኩባንያዎች ውስጥ የመንግስት አክሲዮን ድርሻ አብላጫ እንደሚሆን ጠቁሟል፡፡ከላይ በተጠቀሱት ሜጋ ፕሮጀክቶች እና የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የባለሃብቱ አቅም እየተጠናከረ መሄዱን በማጤን ሙሉ ለሙሉ መንግስት የሚወጣበት ስትራቴጂ መቀመጡም ተጠቁሟል፡፡ ገዥው ፓርቲ እነዚህን የልማት ድርጅቶች ወደ ግል ለማዞር ሶስት አበይት ሁኔታዎችን ታሣቢ በማድረግ መወሠኑንም አስታውቋል፡፡ የመጀመሪያ የውጪ ንግድን ለማሣደግ አጋዥ ይሆናል ከሚል እሣቤ ሲሆን ሁለተኛው ታሣቢ ዜጎችን አካታች የሆነ ሃገራዊ እድገት ማስመዝገብ መሆኑን ይገልፃል፡፡ ሦስተኛው ደግሞ የልማት ድርጅቶች በምርታማነት፣ በአገልግሎት አሠጣጥ ጥራታቸውና አቅማቸው ውጤታማ ሆነው ወደ አለማቀፋዊ ተወዳዳሪነት እንዲያድጉ አጋዥ ይሆናል ከሚል እሳቤ መሆኑን ፓርቲው አስታውቋል፡፡ በዚህ የአክሲዮን ሽያጭ የውጭ ምንዛሬና የካፒታል ገቢ እንደሚገኝም ተጠቁሟል፡፡ የመንግስት ውሣኔን ተከትሎ በበርካታ የአፍሪካ ሃገራት በቴሌኮም ዘርፍ ተሰማርተው የሚገኙት “ኤምቲ ኤን” እና “ቮዳፎን” የተሠኙት ግዙፍ የደቡብ አፍሪካ የግል የቴሌኮም ኩባንያዎች፣ ከቴሌ አክሲዮን ለመግዛት ፍላጎት እንዳላቸውና በጉዳዩ ላይ ከኢትዮጵያ መንግስት ጋር እንደሚነጋገሩ አስታወቋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ገዥው ፓርቲ የመንግስት ድርጅቶች ሽያጭ ላይ ማብራሪያ ሰጠ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> ኤምቲኤን” እና “ቮዳፎን” ከቴሌ ድርሻ ለመግዛት አቅደዋል<br /><br /> የመንግስት ድርጅቶችን ወደ ግል ይዞታ የማዛወሩ ሂደት በጥናት በ...
    0 Comments 0 Shares
  • በዛሬው እለት “የጀግኖች ቀን” በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ኡጋንዳ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሃገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት  ታበረክታለች፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትናንት ጀምሮ በኡጋንዳ ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን ዛሬ በሀገሪቱ በብሪምቦ ክፍለ ግዛት በሚከበረው የጀግኖች ቀን በአል ላይ ለአፍሪካ ነፃነት የታገሉ አፍሪካውያን መሪዎች የሚሸለሙትን ከፍተኛ ሜዳሊያ ይሸለማሉ ተብሏል፡፡ የኡጋንዳ የፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ኃላፊ ሚኒስትር ኢስቴር ማባዮ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለፁት፤ “The Most Excellent Order of the Pearl of Africa The Grand Master” የተሰኘው ልዩ የክብር ሜዳሊያ ለዶ/ር አብይ አህመድ የሚበረከተው ለሃገር ሰላምና ለዜጎች ለሰጡት ክብር እውቅና እንዲሆን ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የክብር ሜዳሊያው ለኢኳቶሪያል ጊኒው ፕሬዚዳንት ቴዎዶሮ ባሳንጎ መሰጠቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ዶ/ር አብይ ሁለተኛው ተሸላሚ የሃገር መሪ ይሆናሉ ብለዋል፡፡
    በዛሬው እለት “የጀግኖች ቀን” በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ኡጋንዳ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሃገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት  ታበረክታለች፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ከትናንት ጀምሮ በኡጋንዳ ይፋዊ ጉብኝት እያደረጉ ሲሆን ዛሬ በሀገሪቱ በብሪምቦ ክፍለ ግዛት በሚከበረው የጀግኖች ቀን በአል ላይ ለአፍሪካ ነፃነት የታገሉ አፍሪካውያን መሪዎች የሚሸለሙትን ከፍተኛ ሜዳሊያ ይሸለማሉ ተብሏል፡፡ የኡጋንዳ የፕሬዚዳንት ፅ/ቤት ኃላፊ ሚኒስትር ኢስቴር ማባዮ ለመገናኛ ብዙኃን እንደገለፁት፤ “The Most Excellent Order of the Pearl of Africa The Grand Master” የተሰኘው ልዩ የክብር ሜዳሊያ ለዶ/ር አብይ አህመድ የሚበረከተው ለሃገር ሰላምና ለዜጎች ለሰጡት ክብር እውቅና እንዲሆን ነው ብለዋል፡፡ ከዚህ ቀደም የክብር ሜዳሊያው ለኢኳቶሪያል ጊኒው ፕሬዚዳንት ቴዎዶሮ ባሳንጎ መሰጠቱን የጠቀሱት ሚኒስትሩ፤ ዶ/ር አብይ ሁለተኛው ተሸላሚ የሃገር መሪ ይሆናሉ ብለዋል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ጠ/ሚ ዐቢይ ዛሬ በኡጋንዳ የክብር ሜዳሊያ ይሸለማሉ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">በዛሬው እለት “የጀግኖች ቀን” በታላቅ ድምቀት የምታከብረው ኡጋንዳ፤ ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ የሃገሪቱን ከፍተኛ የክብር ሽልማት ታበረክታለች፡፡ &...
    0 Comments 0 Shares
  • የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ግጭትን የዳኘው የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለህዝብ በውሣኔ መቅረብ ነበረበት ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ በተግባራዊነቱ ላይ ገዥው ፓርቲ ብቻውን መወሠን አይችልም ብለዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሠጠው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ)፤ የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ መደረጉ ከሁለቱ ህዝቦች ግንኙነትና ከኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ጥቅም አንፃር ተገቢ መሆኑን ገልፆ፤ “ነገር ግን ኢህአዴግ ብቻውን ይህን የሉአላዊነት ጉዳይ የመወሠን ስልጣን ማን ሠጠው?” ሲል ጠይቋል፡፡ፓርቲው በጉዳዩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ወይም የሚኒስትሮች ም/ቤት ተወያይቶ ሊወስንበት ይገባ ነበር ብሏል፡፡የኢህአዴግ ውሳኔ የህዝብ የስልጣን ባለቤትነትና የአካሄድ ጥያቄ ያስነሣል ያለው ኢራፓ እንዲህ አይነቱ የሃገር ሉአላዊነትና ጥቅም ጉዳይ ለህዝብ ውሣኔ መቅረብ እንዳለበት አስገንዝቧል፡፡መኢአድ እና ኦፌኮም ተመሳሳይ አቋም ያራመዱ ሲሆን አረና በበኩሉ ተቃውሞውን በተለያዩ ከተሞች በሚያደርገው ሠልፍ እንደሚገልፅ አስታውቋል፡፡በትናንትናው  እለትም የኢሮብ ማህበረሠብ በሠልፍ ተቃውሞ አሠምቷል፡፡
    የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ግጭትን የዳኘው የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለህዝብ በውሣኔ መቅረብ ነበረበት ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ በተግባራዊነቱ ላይ ገዥው ፓርቲ ብቻውን መወሠን አይችልም ብለዋል፡፡ በጉዳዩ ላይ መግለጫ የሠጠው የኢትዮጵያ ራዕይ ፓርቲ (ኢራፓ)፤ የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ መደረጉ ከሁለቱ ህዝቦች ግንኙነትና ከኢትዮጵያ ስትራቴጂካዊ ጥቅም አንፃር ተገቢ መሆኑን ገልፆ፤ “ነገር ግን ኢህአዴግ ብቻውን ይህን የሉአላዊነት ጉዳይ የመወሠን ስልጣን ማን ሠጠው?” ሲል ጠይቋል፡፡ፓርቲው በጉዳዩ ላይ የህዝብ ተወካዮች ም/ቤት ወይም የሚኒስትሮች ም/ቤት ተወያይቶ ሊወስንበት ይገባ ነበር ብሏል፡፡የኢህአዴግ ውሳኔ የህዝብ የስልጣን ባለቤትነትና የአካሄድ ጥያቄ ያስነሣል ያለው ኢራፓ እንዲህ አይነቱ የሃገር ሉአላዊነትና ጥቅም ጉዳይ ለህዝብ ውሣኔ መቅረብ እንዳለበት አስገንዝቧል፡፡መኢአድ እና ኦፌኮም ተመሳሳይ አቋም ያራመዱ ሲሆን አረና በበኩሉ ተቃውሞውን በተለያዩ ከተሞች በሚያደርገው ሠልፍ እንደሚገልፅ አስታውቋል፡፡በትናንትናው  እለትም የኢሮብ ማህበረሠብ በሠልፍ ተቃውሞ አሠምቷል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለህዝብ ውሣኔ መቅረብ አለበት ተባለ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">የኢትዮጵያና የኤርትራ የድንበር ግጭትን የዳኘው የአልጀርሡ ስምምነት ተግባራዊ ከመደረጉ በፊት ለህዝብ በውሣኔ መቅረብ ነበረበት ያሉት ተቃዋሚ ፓርቲዎች፤ በተግባራዊ...
    0 Comments 0 Shares
  • • “ሥራቸው የሞራል ልዕልና መፍጠር ነው፡፡ የሌብነት ምሽግ መኾን አይችሉም፤”• “ሃይማኖት በመንግሥት፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም የሚለው ሚዛን ያስፈልገዋል፤”    የሃይማኖት ተቋማት በውስጣቸው የተሰገሰገውን የሌብነት ድር በመበጣጠስ፣የሞራል አስተማሪነታቸውን በተግባር እንዲያሳዩ ያስገነዘቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ከእንግዲህ መንግሥታቸው  በተቋማቱ ውስጥ የሚፈጸምን ዘረፋና ሌብነት በቸልታ እንደማያልፈው አስጠነቀቁ፡፡“ሃይማኖት በመንግሥት፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም፤”የሚለው የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ ትክክለኛ መርሕ ቢኾንም፣ የሃይማኖት ተቋማት የሚሰበስቡት መባ እና ዘካ የሕዝብ ሀብት እስከኾነ ድረስ መንግሥት አጠቃቀሙን የመቆጣጠር ርምጃ እንደሚወስድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡የሃይማኖት ተቋማት ገንዘብ የሕዝብ ሀብት እንደኾነና በየትኛውም ዓለም ኦዲት እንደሚደረጉ የጠቀሱት ዶ/ር ዐቢይ፣ትንሽ የሌብነት ምልክት ካዩ ፈቃዳቸውን እስከመቀማት እንደሚደርሱ አስረድተዋል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ከመሬት ጀምሮ ለመንግሥት ለሚያቀርቡት ጥያቄ ባለሥልጣናቱ በእኩልነት ምላሽ መስጠት የሚገባቸውን ያህል፣ በአጸፌታው የመንግሥት ጥያቄ “ምከሩ፤ ገሥጹ፤ ሰላም አምጡ” በማለት ብቻ እንደማይወሰንና እንደማይቀጥል አስረድተዋል፡፡ “በዕለት ተዕለት የሃይማኖት ሥራ መንግሥት አይገባም፤ በመንግሥት የዕለት ተዕለት ሥራ ሃይማኖት አይገባም፤ ግን ደግሞ ቀይ መሥመርና ድንበራችን ሁሌ የቆመና የማይገናኝ አይደለም፤” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አጠቃላይ መርሑ ትክክል ቢኾንም ዘወትር እንደማይሠራና ሚዛን እንደሚያስፈልገው አስገንዝበዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም፣“የሃይማኖት ተቋማት ዋነኛ ሥራቸው፣የሞራል ልዕልና መፍጠር ነው፤ የሌብነት ምሽግ መኾን አይችሉም፤ የለባቸውም፤ አላግባብ መባ እየሰበሰቡ ምን ላይ እንዳዋሉት የማይታወቅ ከኾነ ከእነርሱ የሚጠበቀው የሞራል ልዕልና ይጠፋና የሚያስተምሩትም ምእመን ሌባ ይኾናል፤”በማለት በውስጣቸው የተሰገሰገውን የሌብነት ድር በመበጣጠስ እንዲሁም ሃይማኖት በጥበብና በዕውቀት በባለሥልጣናት ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ በመጠቀም፣ መንግሥትን በተግባር ለማስተማር ቀዳሚውን ድርሻ እንዲወስዱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ፣ በሼራተን አዲስ የተካሔደውን 4ኛውን ሀገር አቀፍ የፀረ ሙስና ጥምረት ጠቅላላ ጉባኤ በንግግር የከፈቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣መንግሥታዊና ሕዝባዊ ተቋማትን ከተደራጁ ሌቦች ለመከላከልና ለማጠናከር የሚደረገው ትግል፣ በመንግሥት ብቻ ከዳር የማይደርስ በመኾኑ፤ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ ሲቪል ማኅበራት፣ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ግለሰቦች፣ ዘርፎ መክበርንና ሰርቆ አለማፈርን የሚያበረታታውን ባህልና አስተሳሰብ እያወገዙና እያጋለጡ በምሳሌነት በመዋጋት ለሕዝቡ ትምህርት እንዲኾኑ ጠይቀዋል - “እስኪ ምሳሌ ኾናችሁ ተገኙ፤ምሳሌ ኾናችሁም ታገሉ፤የሠራችሁትንም ለትምህርት እንዲኾን ለሕዝብ አሳዩ፡፡”
    • “ሥራቸው የሞራል ልዕልና መፍጠር ነው፡፡ የሌብነት ምሽግ መኾን አይችሉም፤”• “ሃይማኖት በመንግሥት፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም የሚለው ሚዛን ያስፈልገዋል፤”    የሃይማኖት ተቋማት በውስጣቸው የተሰገሰገውን የሌብነት ድር በመበጣጠስ፣የሞራል አስተማሪነታቸውን በተግባር እንዲያሳዩ ያስገነዘቡት ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ከእንግዲህ መንግሥታቸው  በተቋማቱ ውስጥ የሚፈጸምን ዘረፋና ሌብነት በቸልታ እንደማያልፈው አስጠነቀቁ፡፡“ሃይማኖት በመንግሥት፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም፤”የሚለው የሕገ መንግሥቱ ድንጋጌ ትክክለኛ መርሕ ቢኾንም፣ የሃይማኖት ተቋማት የሚሰበስቡት መባ እና ዘካ የሕዝብ ሀብት እስከኾነ ድረስ መንግሥት አጠቃቀሙን የመቆጣጠር ርምጃ እንደሚወስድ ጠቅላይ ሚኒስትሩ ጠቁመዋል፡፡የሃይማኖት ተቋማት ገንዘብ የሕዝብ ሀብት እንደኾነና በየትኛውም ዓለም ኦዲት እንደሚደረጉ የጠቀሱት ዶ/ር ዐቢይ፣ትንሽ የሌብነት ምልክት ካዩ ፈቃዳቸውን እስከመቀማት እንደሚደርሱ አስረድተዋል፡፡ የሃይማኖት ተቋማት ከመሬት ጀምሮ ለመንግሥት ለሚያቀርቡት ጥያቄ ባለሥልጣናቱ በእኩልነት ምላሽ መስጠት የሚገባቸውን ያህል፣ በአጸፌታው የመንግሥት ጥያቄ “ምከሩ፤ ገሥጹ፤ ሰላም አምጡ” በማለት ብቻ እንደማይወሰንና እንደማይቀጥል አስረድተዋል፡፡ “በዕለት ተዕለት የሃይማኖት ሥራ መንግሥት አይገባም፤ በመንግሥት የዕለት ተዕለት ሥራ ሃይማኖት አይገባም፤ ግን ደግሞ ቀይ መሥመርና ድንበራችን ሁሌ የቆመና የማይገናኝ አይደለም፤” ያሉት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣ አጠቃላይ መርሑ ትክክል ቢኾንም ዘወትር እንደማይሠራና ሚዛን እንደሚያስፈልገው አስገንዝበዋል፡፡ጠቅላይ ሚኒስትሩ አያይዘውም፣“የሃይማኖት ተቋማት ዋነኛ ሥራቸው፣የሞራል ልዕልና መፍጠር ነው፤ የሌብነት ምሽግ መኾን አይችሉም፤ የለባቸውም፤ አላግባብ መባ እየሰበሰቡ ምን ላይ እንዳዋሉት የማይታወቅ ከኾነ ከእነርሱ የሚጠበቀው የሞራል ልዕልና ይጠፋና የሚያስተምሩትም ምእመን ሌባ ይኾናል፤”በማለት በውስጣቸው የተሰገሰገውን የሌብነት ድር በመበጣጠስ እንዲሁም ሃይማኖት በጥበብና በዕውቀት በባለሥልጣናት ላይ የሚፈጥረውን ተጽዕኖ በመጠቀም፣ መንግሥትን በተግባር ለማስተማር ቀዳሚውን ድርሻ እንዲወስዱ ጥሪያቸውን አቅርበዋል፡፡ ባለፈው ረቡዕ፣ በሼራተን አዲስ የተካሔደውን 4ኛውን ሀገር አቀፍ የፀረ ሙስና ጥምረት ጠቅላላ ጉባኤ በንግግር የከፈቱት ጠቅላይ ሚኒስትሩ፣መንግሥታዊና ሕዝባዊ ተቋማትን ከተደራጁ ሌቦች ለመከላከልና ለማጠናከር የሚደረገው ትግል፣ በመንግሥት ብቻ ከዳር የማይደርስ በመኾኑ፤ የሃይማኖት አባቶችን ጨምሮ ሲቪል ማኅበራት፣ የአገር ሽማግሌዎችና ታዋቂ ግለሰቦች፣ ዘርፎ መክበርንና ሰርቆ አለማፈርን የሚያበረታታውን ባህልና አስተሳሰብ እያወገዙና እያጋለጡ በምሳሌነት በመዋጋት ለሕዝቡ ትምህርት እንዲኾኑ ጠይቀዋል - “እስኪ ምሳሌ ኾናችሁ ተገኙ፤ምሳሌ ኾናችሁም ታገሉ፤የሠራችሁትንም ለትምህርት እንዲኾን ለሕዝብ አሳዩ፡፡”
    ADDISADMASSNEWS.COM
    ሃይማኖት ተቋማት ሙስና መንግሥት እርምጃ ይወስዳል - ጠ/ሚኒስትሩ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;">• “ሥራቸው የሞራል ልዕልና መፍጠር ነው፡፡ የሌብነት ምሽግ መኾን አይችሉም፤”<br />• “ሃይማኖት በመንግሥት፣ መንግሥት በሃይማኖት ጣልቃ አይገባም የ...
    0 Comments 0 Shares
  •  የሆቴልና ሪዞርቶቹን ቁጥር በ6 ዓመት ውስጥ 20 ለማድረስ አቅዷል                   በአርባ ምንጭ የተገነባው 400 ሚ. ብር የወጣበት ኃይሌ ሪዞርት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ግንባታው አንድ ዓመት ከሰባት ወር የፈጀ ሲሆን ሁሉም ስራው ተሰርቶ የተጠናቀቀው በአገር ውስጥ ባለሙያዎች መሆኑን ሻለቃ አትሌት ኃይሉ ገ/ሥላሴና የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች የሆስፒታሊቲ ግሩፕ ዳይሬክተር አቶ መልካሙ መኮንን ከትላንት በስቲያ በዓለም ሲኒማ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ ኃይሌ በቀጣይ 6 ዓመታት ውስጥ የሆቴሎቹን ቁጥር 20 ለማድረስ ማቀዱንም ገልጿል፡፡ ሆቴሉ በአርባ ምንጭ በጣም የሚያምር እይታ ላይ የተሰራና በ42 ሸህ ስኩየር ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን ለከተማዋ የመጀመሪያ ሪዞርት መሆኑ ታውቋል፡፡ ባለ አራት ኮከብ ሪዞርቱ 110 ደረጃቸውን የጠበቁ የመኝታ ክፍሎች፣ አራት የተለያየ መጠን ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣ አራት የምግብ አዳራሾች፣ እንግዶችና የአካባቢው ህዝብ ጤናውን የሚጠብቅበት ጂምናዚየም፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የህፃናት መጫወቻ፣ መለስተኛ ኳስ ሜዳ፣ አባያና ጫሞንና የእግዜር ድልድይን ጨምሮ የአካባቢውን ልዩ ተፈጥሮ መመልከቻ ማማ፣ ስፓ እንዲሁም ለባንክ፣ ለስጦታ እቃ መሸጫ፣ ለቢሮና መሰል አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችና በቂ የመኪና ማቆሚያን አካትቶ የተገነባ መሆኑን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ  አስታውቋል፡፡ ሪዞርቱ በሙሉ አቅሙ ስራ መጀመሩን የገለፀው ኃይሌ፣ ለ300 ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠሩንና ከሰራተኞቹ 95 በመቶ ያህሉ የአካባቢው ነዋሪዎች መሆናቸውን ጠቁሞ፣ ይህም የኃይሌ አለም ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ጠቅላላ ሰራተኞችን ቁጥር ወደ 2300 ከፍ እንዳደረገው በዕለቱ ተናግሯል፡፡ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶችን ለየት የሚያደርጋቸው ልክ እንደነ ሂልተን ሸራተንና ማሪዎት ቼይን አገር በቀል ሆቴልና ሪዞርት በመሆኑ ነው ያለው ኃይሌ፤ በቀጣዮቹ 6 ዓመታት የሆቴልና ሪዞርቶቹን ቁጥር 20 ለማድረስ መታቀዱን ገልፆ በአዲስ አበባ የባለ 5 ኮከብ ሆቴል ግንባታ መጀመሩን፣ በኮንሶ  በደብረብርሃንና ሶዶ ሆቴልና ሪዞርቶችን ለመገንባት ቦታ ወስዶ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግሯል፡፡ ኃይሌ አለም ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ግሩፕ በ1992 ዓ.ም በ50 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመ ኩባንያ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በግብርና (በቡና ማር)፣ በትምህርት፣ በሪል እስቴት፣ በማዕድንና በተለይም በሆቴሉ ዘርፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡
     የሆቴልና ሪዞርቶቹን ቁጥር በ6 ዓመት ውስጥ 20 ለማድረስ አቅዷል                   በአርባ ምንጭ የተገነባው 400 ሚ. ብር የወጣበት ኃይሌ ሪዞርት አገልግሎት መስጠት ጀመረ፡፡ ግንባታው አንድ ዓመት ከሰባት ወር የፈጀ ሲሆን ሁሉም ስራው ተሰርቶ የተጠናቀቀው በአገር ውስጥ ባለሙያዎች መሆኑን ሻለቃ አትሌት ኃይሉ ገ/ሥላሴና የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶች የሆስፒታሊቲ ግሩፕ ዳይሬክተር አቶ መልካሙ መኮንን ከትላንት በስቲያ በዓለም ሲኒማ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ አስታውቀዋል፡፡ ኃይሌ በቀጣይ 6 ዓመታት ውስጥ የሆቴሎቹን ቁጥር 20 ለማድረስ ማቀዱንም ገልጿል፡፡ ሆቴሉ በአርባ ምንጭ በጣም የሚያምር እይታ ላይ የተሰራና በ42 ሸህ ስኩየር ሜትር ላይ ያረፈ ሲሆን ለከተማዋ የመጀመሪያ ሪዞርት መሆኑ ታውቋል፡፡ ባለ አራት ኮከብ ሪዞርቱ 110 ደረጃቸውን የጠበቁ የመኝታ ክፍሎች፣ አራት የተለያየ መጠን ያላቸው የስብሰባ አዳራሾች፣ አራት የምግብ አዳራሾች፣ እንግዶችና የአካባቢው ህዝብ ጤናውን የሚጠብቅበት ጂምናዚየም፣ የመዋኛ ገንዳ፣ የህፃናት መጫወቻ፣ መለስተኛ ኳስ ሜዳ፣ አባያና ጫሞንና የእግዜር ድልድይን ጨምሮ የአካባቢውን ልዩ ተፈጥሮ መመልከቻ ማማ፣ ስፓ እንዲሁም ለባንክ፣ ለስጦታ እቃ መሸጫ፣ ለቢሮና መሰል አገልግሎት የሚውሉ ክፍሎችና በቂ የመኪና ማቆሚያን አካትቶ የተገነባ መሆኑን ሻለቃ ኃይሌ ገ/ሥላሴ  አስታውቋል፡፡ ሪዞርቱ በሙሉ አቅሙ ስራ መጀመሩን የገለፀው ኃይሌ፣ ለ300 ሰራተኞች የስራ እድል መፍጠሩንና ከሰራተኞቹ 95 በመቶ ያህሉ የአካባቢው ነዋሪዎች መሆናቸውን ጠቁሞ፣ ይህም የኃይሌ አለም ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ጠቅላላ ሰራተኞችን ቁጥር ወደ 2300 ከፍ እንዳደረገው በዕለቱ ተናግሯል፡፡ የኃይሌ ሆቴልና ሪዞርቶችን ለየት የሚያደርጋቸው ልክ እንደነ ሂልተን ሸራተንና ማሪዎት ቼይን አገር በቀል ሆቴልና ሪዞርት በመሆኑ ነው ያለው ኃይሌ፤ በቀጣዮቹ 6 ዓመታት የሆቴልና ሪዞርቶቹን ቁጥር 20 ለማድረስ መታቀዱን ገልፆ በአዲስ አበባ የባለ 5 ኮከብ ሆቴል ግንባታ መጀመሩን፣ በኮንሶ  በደብረብርሃንና ሶዶ ሆቴልና ሪዞርቶችን ለመገንባት ቦታ ወስዶ እንቅስቃሴ መጀመሩን ተናግሯል፡፡ ኃይሌ አለም ኢንተርናሽናል ቢዝነስ ግሩፕ በ1992 ዓ.ም በ50 ሚሊዮን ብር ካፒታል የተቋቋመ ኩባንያ ሲሆን በአሁኑ ሰዓት በግብርና (በቡና ማር)፣ በትምህርት፣ በሪል እስቴት፣ በማዕድንና በተለይም በሆቴሉ ዘርፍ ከፍተኛ እንቅስቃሴ እያደረገ ይገኛል፡፡
    ADDISADMASSNEWS.COM
    በ400 ሚ. ብር የተገነባው ሀይሌ፣ ሪዞርት አርባ ምንጭ ሥራ ጀመረ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> የሆቴልና ሪዞርቶቹን ቁጥር በ6 ዓመት ውስጥ 20 ለማድረስ አቅዷል<br /> <br /> በአርባ ምንጭ የተገነባው 400 ሚ. ብር የወጣበት ኃይ...
    0 Comments 0 Shares
  •  ለአራት ዓመት በፊት ቦሌ አካባቢ “የአደይ አበባ” በሚል ስያሜ ለሚገነባው ብሔራዊ ስታዲየም ከመኖሪያቸው የተነሱ 355 አባወራዎች እስካሁን ምትክ ቦታና ካሳ አልተሰጠንም ሲሉ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ በግንባታ ላይ የሚገኘው ብሔራዊ ስታዲየም ሲጠናቀቅ 60ሺህ ተመልካቾችን ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አባወራዎቹ መሬቱ ለልማት ይፈለጋል ተብለው እንዲነሱ ሲደረግ አዲስ በሚዘጋጅ መመሪያ መሰረት፤ ምትክ ቦታና ካሳ ይሰጣችኋል፤ በሚል መሬቱን በኃይል እንዲለቁ ቢደረግም ላለፉት 4 ዓመታት ከ38 በላይ የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቢመላለሱም ሰሚ ማጣታቸውን ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ነዋሪቹ በአሁኑ ወቅት ከዘመድ ተጠግተውና አነስተኛ ቤቶችን በመከራየት ጎስቋላ ኑሮ እየመሩ መሆኑን በማስረዳት፣ መንግስት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ አቤቱታቸውንም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በደብዳቤ ያስገቡ ሲሆን በደብዳቤያቸው እንደገለፁት፤ በቦታው ላይ ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ ይኖሩ እንደነበር ጠቁመው፤፤ ቦታው ለልማት ይፈለጋል ሲባልም፣ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 አስተዳደር፣ ለእያንዳንዳቸው 75 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ምትክ ቦታ ከእነካሳው እንደሚሰጣቸው ቃል ተገብቶላቸው ነበር፡፡ “ካሣና ምትክ ቦታ ይሰጣችኋል፤ ኮንዶሚኒየም ቤት እንዳትመዘገቡ ተብለን እድላችንን እንድናሳልፍም ተደርገናል” የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በ2003 ዓ.ም የተነሳውን የአየር ካርታ ምስል በአቤቱታቸው ላይ በማያያዝ፣ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ጉዳዩን መርምረው መፍትሄ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል፡፡   
     ለአራት ዓመት በፊት ቦሌ አካባቢ “የአደይ አበባ” በሚል ስያሜ ለሚገነባው ብሔራዊ ስታዲየም ከመኖሪያቸው የተነሱ 355 አባወራዎች እስካሁን ምትክ ቦታና ካሳ አልተሰጠንም ሲሉ አቤቱታ አቀረቡ፡፡ በግንባታ ላይ የሚገኘው ብሔራዊ ስታዲየም ሲጠናቀቅ 60ሺህ ተመልካቾችን ይይዛል ተብሎ ይጠበቃል፡፡ አባወራዎቹ መሬቱ ለልማት ይፈለጋል ተብለው እንዲነሱ ሲደረግ አዲስ በሚዘጋጅ መመሪያ መሰረት፤ ምትክ ቦታና ካሳ ይሰጣችኋል፤ በሚል መሬቱን በኃይል እንዲለቁ ቢደረግም ላለፉት 4 ዓመታት ከ38 በላይ የተለያዩ የመንግስት መስሪያ ቤቶች ቢመላለሱም ሰሚ ማጣታቸውን ለአዲስ አድማስ አስረድተዋል፡፡ ነዋሪቹ በአሁኑ ወቅት ከዘመድ ተጠግተውና አነስተኛ ቤቶችን በመከራየት ጎስቋላ ኑሮ እየመሩ መሆኑን በማስረዳት፣ መንግስት አፋጣኝ ምላሽ እንዲሰጣቸው ጠይቀዋል፡፡ አቤቱታቸውንም ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በደብዳቤ ያስገቡ ሲሆን በደብዳቤያቸው እንደገለፁት፤ በቦታው ላይ ከ1995 ዓ.ም ጀምሮ ይኖሩ እንደነበር ጠቁመው፤፤ ቦታው ለልማት ይፈለጋል ሲባልም፣ የቦሌ ክ/ከተማ ወረዳ 3 አስተዳደር፣ ለእያንዳንዳቸው 75 ካሬ ሜትር የመኖሪያ ቤት መስሪያ ምትክ ቦታ ከእነካሳው እንደሚሰጣቸው ቃል ተገብቶላቸው ነበር፡፡ “ካሣና ምትክ ቦታ ይሰጣችኋል፤ ኮንዶሚኒየም ቤት እንዳትመዘገቡ ተብለን እድላችንን እንድናሳልፍም ተደርገናል” የሚሉት ቅሬታ አቅራቢዎቹ፤ በ2003 ዓ.ም የተነሳውን የአየር ካርታ ምስል በአቤቱታቸው ላይ በማያያዝ፣ ጠቅላይ ሚኒስተሩ ጉዳዩን መርምረው መፍትሄ እንዲሰጧቸው ጠይቀዋል፡፡   
    ADDISADMASSNEWS.COM
    የስታዲየም ግንባታ ተነሺዎች ካሳና ምትክ ቦታ አልተሰጠንም ሲሉ አማረሩ - Addis Admass Newspaper | Amharic news | Ethiopian news
    <p style="text-align: justify;"> ለአራት ዓመት በፊት ቦሌ አካባቢ “የአደይ አበባ” በሚል ስያሜ ለሚገነባው ብሔራዊ ስታዲየም ከመኖሪያቸው የተነሱ 355 አባወራዎች እስካሁን ምትክ ቦታና ካሳ አል...
    0 Comments 0 Shares
  • አዲሶቹ የመከላከያና የደኅንነት አለቆች
    ብሩክ አብዱ
    Sun, 06/10/2018 - 09:11
    አዲሶቹ የመከላከያና የደኅንነት አለቆች ብሩክ አብዱ Sun, 06/10/2018 - 09:11
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    አዲሶቹ የመከላከያና የደኅንነት አለቆች | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    ጠቅላይ ሚኒስትር ዓብይ አህመድ (ዶ/ር) ሐሙስ ግንቦት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ብዙ ጊዜ በማያጋጥም ክስተት፣ ሁለት ከፍተኛ የአገሪቱን የመከላከያና የደኅንነት ተቋማት ኃላፊዎችን በአንድ ቀን ተክተዋል፡፡ ጠቅላይ ሚኒስትሩ የአገር መከላከያ ሠራዊት ጠቅላይ ኤታ ማዦር ሹም የነበሩትን ጄኔራል ሳሞራ የኑስን በክብር ሸኝተው፣ ጄኔራል ሰዓረ መኰንንን በምትካቸው ሾመዋል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • የገንዘብ እጥረት ቀውስ በኢኮኖሚው ላይ ሥጋት መደቀኑን መንግሥት አመነ
    ዮሐንስ አንበርብር
    Sun, 06/10/2018 - 09:07
    የገንዘብ እጥረት ቀውስ በኢኮኖሚው ላይ ሥጋት መደቀኑን መንግሥት አመነ ዮሐንስ አንበርብር Sun, 06/10/2018 - 09:07
    WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
    የገንዘብ እጥረት ቀውስ በኢኮኖሚው ላይ ሥጋት መደቀኑን መንግሥት አመነ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
    የአገሪቱን ኢኮኖሚ ቀጣይነት ለማረጋገጥ የገንዘብ እጥረት ቀውስ እንደገጠመው፣ እጥረቱ በፍጥነት መፍትሔ ካልተገኘለት ኢኮኖሚውን በመጉዳት ማኅበራዊ ችግር ሊፈጥር እንደሚችል መንግሥት በይፋ አስታወቀ፡፡ ይህንን የተናገሩት የገንዘብና ኢኮኖሚ ትብብር ሚኒስትሩ አብርሃም ተከስተ (ዶ/ር)፣ የፌዴራል መንግሥትን የ2011 ዓ.ም. ረቂቅ በጀት ሐሙስ ግንቦት 30 ቀን 2010 ዓ.ም. ለፓርላማ ባቀረቡበት ወቅት ነው፡፡
    0 Comments 0 Shares