0 Comments
0 Shares
Directory
-
Please log in to like, share and comment!
-
AMHARIC.VOANEWS.COMየእስራኤል ጦር በሶስተኛው ቀን የዌስት ባንክ ወረራው ጂኒንን አጠቃየእስራኤል ጦር በፍልስጤም ግዛት ዌስት ባንክ ሶስተኛውን ቀን ባስቆጠረው ጥቃት ጄኒን ከተማ ላይ የአየር ድብደባ ፈፅሟል ሲሉ ባለሥልጣናት ተናገሩ፡፡ የእስራኤል ጦር ካላፈው ማክሰኞ ጀምሮ 19 ሰዎች የተገደሉባቸው ጥቃቶች “የሽብረተኞች ምሽግ” ላይ ያነጣጠሩ” እና በሰሜናዊ ዌስት ባንክ የተካሄዱ ጥቃቶችን ለመከላከል ያለሙ መሆናቸውን አስታውቋል፡፡ እንዲህ ያሉት ጥቃቶች ወራትን ባስቆጠረው የእስራኤልና ሀማስ ግጭት የተለመዱ ቢሆንም በዌስት ባንክ ብዙ ጊዜ የሚታዩ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMቻይና በአፍሪካ የመሠረተ ልማት ግንባታ ትብብር ውጤቶችን ሪፖርት አሳተመችቻይና በቤልት ኤንድ ሮድ በተባለው የመሠረት ልማት ግንባታ (BRI) ማዕቀፍ ውስጥ በቻይና-አፍሪካ የትብብር ውጤቶችን የያዘ ሪፖርት አሳተመች። ሪፖርቱ 52 የአፍሪካ ሀገራት እና የአፍሪካ ህብረት ከቻይና ጋር በቤልት ኤንድ ሮድ ትብብር የመግባቢያ ስምምነት ተፈራርመዋል ብሏል። “ቻይና እና አፍሪካ የመሠረተ ልማት ትስስራቸውን ወደ አዲስ ደረጃ ከፍ አድርገዋል” ይላል ዘገባው:: የቻይና ኩባንያዎች ከ10,000 ኪሎ ሜትር በላይ የባቡር መስመር ዝርጋታ፣ ወደ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየቀድሞ የሩሲያ ምክትል የመከላከያ ሚኒስትር ታሰሩየቀድሞው የመከላከያ ምክትል ሚኒስትር ፓቬልፖፖቭ በማጭበርበር ወንጀል ተጠርጥረው ትላንት ሐሙስ በቁጥጥር ስር መዋላቸውን የሩሲያ መንግስት ዜና ማሰራጫ ዘግቧል። ፖፖቭ በተጠረጠሩበት ወንጀል ክስ ከተመሰረተባቸው እና ከተፈረደባቸው እስከ 10 አመት እስራት ይጠብቃቸዋል። በፖፖቭ ላይ የተመሰረተው ክስ፣ሞስኮ በሚገኘው የፓትሪዮትፓርክ ውስጥ ከሚገኙ የንግድ እንቅስቃሴዎች ጋር የተያያዘ ነው፡፡ በወጣት ሩሲያውያን መካከል የሀገር ፍቅር ስሜትን ለመፍጠር የተቋቋመው...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMየዩናይትድ ስቴትስ በደቡብ ሱዳን ባለስልጣናት ላይ ማዕቀብ ጣለችዩናይትድ ስቴትስ የመንግስት ኃላፊዎችን ጨምሮ፣ ለሰብአዊ ርዳታ እጅግ ደሃ ወደ ሆነቸው ሀገር እንዳይገባ እንቅፋት ሆነዋል ባለቻቸው ቁጥራቸው በውል ባልታወቀ ደቡብ ሱዳናውያን ላይ የቪዛ ማዕቀብ መጣሏን ዛሬ ዓርብ አስታወቀች፡፡ የዩናትይድ ስቴትስ የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ዛሬ ባወጣው መግለጫ “እኤአ በ2011 ነጻነቷን ከሱዳን የተቀዳጀችው ደቡብ ሱዳን ለአምስት ዓመት የዘለቀው የርስ በርስ ጦርነት እኤኤ በ2018 በተካሄደው የሰላም ስምምነት ካበቃ በኋላ የደቡብ ሱዳን...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMኢትዮጵያ በዐዲሱ የሶማሊያ የሰላም ተልዕኮ ውስጥ የመካተት ፍላጎት እንዳላት ገለጸችኢትዮጵያ፣ በዐዲሱ የሶማሊያ የሰላም ተልዕኮ ውስጥ በመካተት ሽብርተኝነትን የመዋጋትና የሶማሊያን መንግሥት የመርዳት ፍላጎት እንዳላት አስታውቃለች፡፡ የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ ዛሬ ዐርብ፣ ነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋራ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከርና ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው፤ ብለዋል። የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፣...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበሰሜን ሸዋ ዞን ታግተው ከነበሩት 52 መንገደኞች ስምንቱ አሁንም አልተለቀቁምትላንት ኀሙስ፣ ከዐዲስ አበባ ወደ ደብረ ማርቆስ ከተማ በሕዝብ ማመላለሻ አውቶብስ ሲጓዙ የነበሩ 52 ሰዎች፣ በታጣቂዎች ታግተው እንደነበር የገለጸው በኦሮሚያ ክልል የሰሜን ሸዋ ዞን አስተዳደር፣ ኾኖም አብዛኛዎቹ ወዲያውኑ አምልጠው ስምንት ተሳፋሪዎች ብቻ መቅረታቸውን አስታውቋል።። በኦሮሚያ ክልል፣ በገብረ ጉራቻ እና ቱሉ ሚልኪ ከተሞች መካከል ባለ ቦታ ላይ፣ ከማሽላ ማሳ ውስጥ የወጡ ታጣቂዎች አውቶብሱን አስቁመው፣ አሽከርካሪውን ጨምሮ 52 ተሳፋሪዎችን ወደ ጫካ...0 Comments 0 Shares -
AMHARIC.VOANEWS.COMበምዕራብ ጎንደር ዞን ሁለት የስደተኛ መጠለያዎች መዘጋታቸውን ተመድ አስታወቀበዐማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የነበሩት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአውላላ እና የኩመር የስደተኛ መጠለያዎች መዘጋታቸውን፣ የድርጅቱ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በምኅጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡ ሁለቱም መጠለያዎች የጸጥታ ችግር እንደነበረባቸው፣ የስደተኞች ተቋሙ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡ የሱዳንን ጦርነት ሸሽተው እየመጡ ያሉትን ስደተኞች ለማስጠለልም፣ ከኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ጋራ በመተባበር፣...0 Comments 0 Shares