• እየሩሳሌም — እስራኤል የ6 ታጋቾችን አስክሬን ጋዛ ውስጥ  ማግኘቷን በዛሬው ዕለት አስታወቀች። ከእነዚህ መካከል በሀማስ ከተያዙ እና በእጅጉ ታዋቂ ከነበሩት መካከል አንዱ የነበረው ወጣቱ እስራኤላዊ-አሜሪካዊ ኸርሽ ጎልድበርግ- ፖሊን ይገኝበታል ።ከዓለም መሪዎች ጋር የተገናኙት ወላጆቹ ነጻ እንዲወጣ ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል ።  


    የእስራኤል ጦር በስፍራው  ከመድረሱ ጥቂት ቀደም ብሎ ስድስቱም ታጋቾች  መገደላቸውን አስታውቋል። የታጋቾቹ አስክሬን መገኘት ፣ ብዙ እስራኤላውያን ለ10 ወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማቆም ከሃማስ ጋር በሚደረግ  ስምምነት ታጋቾችን  በህይወት መመለስ ባለመቻላቸው ተጠያቂ ባደረጓቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ላይ ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲካሄድ የሚጠይቁ ጥሪዎችን ቀስቀሷል ።ድርድሩ ካለ አንዳች ስምምነት ለወራት መጓተቱ ይታወሳል ።




    ኔትንያሁ  " ርህራሄ በጎደለው መንገድ " ታጋቾቹን ገድሏል ያሉት ሀማስን ሀገራቸው ተጠያቂ እንደምታደርግ ተናግረዋል። " ታጋቾችን የገደለ ስምምነትን አይሻም " ያሉት ኔትንያሁ ፣ታጣቂውን ቡድን ድርድሩን በማደናቀፍም ከሰዋል ።  


    ታጣቂዎቹ የ23 ዓመቱን ኸርሽ  ጎልድበርግ-ፖሊን እና አራት አጋቾችን  ያፈኗቸው ጥቅምት 7 ሀማስ በደቡብ እስራኤል እየተከናወነ በነበረ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ጥቃት በከፈተበት ወቅት ሲሆን ፣ ይህ ክስተት የጦርነቱ መነሾ ሆኗል ።


    ከበርክሌይ፣ ካሊፎርኒያ የመጣው ኸርሽ ፣ በፈንጂ ጥቃት ምክንያት ግራ አጇን አጥቷል። በሚያዚያ ወር ላይ ሀማስ ባሰራጨው ቪዲዮ ላይ ኸርሽ በህይወት መኖሩ እና ግራ እጁን እንዳጣ የታየ ሲሆን ፣ በምላሹ መንግስት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ የበለጠ እንዲሰራ የሚያሳስብ አዲስ ተቃውሞ በእስራኤል አስነስቷል።

     

    የእስራኤል ጦር በተጨማሪም ፣ከሙዚቃ ዝግጅቱ ላይ የታፈኑት ፣ የ25 ዓመቱ ኦሪ ዳንኢኖ ፣ የ24 ዓመቷ ኤደን የሩሻለሚ ፣ የ27 ዓመቱ አልሞግ ሳሩሲ እና የ33 ዓመቱ አሌክሳንደር ላቦኖቭ ከሟቾች መካከል መሆናቸውን አስታውቋል ። ስድስተኛዋ ሟች የ40 ዓመቷ ካርሜል ጋት ቤሪ ከሚባለው አረሶ አደር ማህበረሰብ የታገተች እንደነበር ተገልጿል ።


    አስክሬኖቹ የተገኙት በደቡብ ጋዛ  በምትገኘው ራፋ ውስጥ ካለ ዋሻ መሆኑን ጦር አስታውቋል ። ዋሻው ከሳምንት በፊት  ካይድ ፋርሃን አልካዲ የተሰኙ የ52 ዓመት ታጋች በሕይወት ከተረፉበት  ስፍራ አንድ ኪሎሜትር ርቆ እንደሚገኝ ተነግሯል ።


    የወታደራዊው  ቃል አቀባይ ሌተናል ኮሎኔል ናዳቭ ሾሻኒ እንዳሉት ሰራዊቱ በአካባቢው ታጋቾች እንዳሉ በወቅቱ ቢያምንም  ነገር ግን የተለየ መረጃ እንዳልበረው ገልጸዋል ።ታጋቾችን ሀማስ እንደገደላቸው ጥርጣሬ እንደሌላቸው ተናግረዋል ።




    ሀማስ ታጋቾችችን ለመልቀቅ እና በምላሹም ጦርነቱ እንዲቆም ፣ የእስራኤል ኃይሎች እንዲወጡ እና ቁልፍ ሚና ያላቸው ተዋጊዎችን ጨምሮ ከፍተኛ ብዛት ያላቸው ፍልስጤማዊያን እስረኞች እንዲለቀቁ መጠየቁ ይታወሳል ።


    አይዛት አል ሪሽቅ የተባሉት የሐማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ፣ሀማስ በሐምሌ ወር እንደተስማማበት የገለጸው እና በአሜሪካ የተደገፈውን  የተኩስ አቁም ሀሳብ እስራኤል ብትቀበል ኖሮ ታጋቾቹ በህይወት ይተርፉ  እንደነበር ተናግረዋል።  የታጋቾቹ ቤተሰቦች ሀገሪቱ ውስጥ የሚደረግ እንቅስቃሴ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል ።


    ኔታንያሁ ሀማስ እስኪጠፋ ድረስ ጦርነቱን እንደሚቀጥል ገልፀው ታጋቾቹን ወደ ቤት ለማምጣት ወታደራዊ ግፊት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል (AP)።

     

    እየሩሳሌም — እስራኤል የ6 ታጋቾችን አስክሬን ጋዛ ውስጥ  ማግኘቷን በዛሬው ዕለት አስታወቀች። ከእነዚህ መካከል በሀማስ ከተያዙ እና በእጅጉ ታዋቂ ከነበሩት መካከል አንዱ የነበረው ወጣቱ እስራኤላዊ-አሜሪካዊ ኸርሽ ጎልድበርግ- ፖሊን ይገኝበታል ።ከዓለም መሪዎች ጋር የተገናኙት ወላጆቹ ነጻ እንዲወጣ ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል ።   የእስራኤል ጦር በስፍራው  ከመድረሱ ጥቂት ቀደም ብሎ ስድስቱም ታጋቾች  መገደላቸውን አስታውቋል። የታጋቾቹ አስክሬን መገኘት ፣ ብዙ እስራኤላውያን ለ10 ወራት የዘለቀውን ጦርነት ለማቆም ከሃማስ ጋር በሚደረግ  ስምምነት ታጋቾችን  በህይወት መመለስ ባለመቻላቸው ተጠያቂ ባደረጓቸው ጠቅላይ ሚኒስትር ቤንጃሚን ኔታንያሁ ላይ ህዝባዊ ተቃውሞ እንዲካሄድ የሚጠይቁ ጥሪዎችን ቀስቀሷል ።ድርድሩ ካለ አንዳች ስምምነት ለወራት መጓተቱ ይታወሳል ። ኔትንያሁ  " ርህራሄ በጎደለው መንገድ " ታጋቾቹን ገድሏል ያሉት ሀማስን ሀገራቸው ተጠያቂ እንደምታደርግ ተናግረዋል። " ታጋቾችን የገደለ ስምምነትን አይሻም " ያሉት ኔትንያሁ ፣ታጣቂውን ቡድን ድርድሩን በማደናቀፍም ከሰዋል ።   ታጣቂዎቹ የ23 ዓመቱን ኸርሽ  ጎልድበርግ-ፖሊን እና አራት አጋቾችን  ያፈኗቸው ጥቅምት 7 ሀማስ በደቡብ እስራኤል እየተከናወነ በነበረ የሙዚቃ ዝግጅት ላይ ጥቃት በከፈተበት ወቅት ሲሆን ፣ ይህ ክስተት የጦርነቱ መነሾ ሆኗል ። ከበርክሌይ፣ ካሊፎርኒያ የመጣው ኸርሽ ፣ በፈንጂ ጥቃት ምክንያት ግራ አጇን አጥቷል። በሚያዚያ ወር ላይ ሀማስ ባሰራጨው ቪዲዮ ላይ ኸርሽ በህይወት መኖሩ እና ግራ እጁን እንዳጣ የታየ ሲሆን ፣ በምላሹ መንግስት ታጋቾቹን ለማስለቀቅ የበለጠ እንዲሰራ የሚያሳስብ አዲስ ተቃውሞ በእስራኤል አስነስቷል።   የእስራኤል ጦር በተጨማሪም ፣ከሙዚቃ ዝግጅቱ ላይ የታፈኑት ፣ የ25 ዓመቱ ኦሪ ዳንኢኖ ፣ የ24 ዓመቷ ኤደን የሩሻለሚ ፣ የ27 ዓመቱ አልሞግ ሳሩሲ እና የ33 ዓመቱ አሌክሳንደር ላቦኖቭ ከሟቾች መካከል መሆናቸውን አስታውቋል ። ስድስተኛዋ ሟች የ40 ዓመቷ ካርሜል ጋት ቤሪ ከሚባለው አረሶ አደር ማህበረሰብ የታገተች እንደነበር ተገልጿል ። አስክሬኖቹ የተገኙት በደቡብ ጋዛ  በምትገኘው ራፋ ውስጥ ካለ ዋሻ መሆኑን ጦር አስታውቋል ። ዋሻው ከሳምንት በፊት  ካይድ ፋርሃን አልካዲ የተሰኙ የ52 ዓመት ታጋች በሕይወት ከተረፉበት  ስፍራ አንድ ኪሎሜትር ርቆ እንደሚገኝ ተነግሯል ። የወታደራዊው  ቃል አቀባይ ሌተናል ኮሎኔል ናዳቭ ሾሻኒ እንዳሉት ሰራዊቱ በአካባቢው ታጋቾች እንዳሉ በወቅቱ ቢያምንም  ነገር ግን የተለየ መረጃ እንዳልበረው ገልጸዋል ።ታጋቾችን ሀማስ እንደገደላቸው ጥርጣሬ እንደሌላቸው ተናግረዋል ። ሀማስ ታጋቾችችን ለመልቀቅ እና በምላሹም ጦርነቱ እንዲቆም ፣ የእስራኤል ኃይሎች እንዲወጡ እና ቁልፍ ሚና ያላቸው ተዋጊዎችን ጨምሮ ከፍተኛ ብዛት ያላቸው ፍልስጤማዊያን እስረኞች እንዲለቀቁ መጠየቁ ይታወሳል ። አይዛት አል ሪሽቅ የተባሉት የሐማስ ከፍተኛ ባለስልጣን ፣ሀማስ በሐምሌ ወር እንደተስማማበት የገለጸው እና በአሜሪካ የተደገፈውን  የተኩስ አቁም ሀሳብ እስራኤል ብትቀበል ኖሮ ታጋቾቹ በህይወት ይተርፉ  እንደነበር ተናግረዋል።  የታጋቾቹ ቤተሰቦች ሀገሪቱ ውስጥ የሚደረግ እንቅስቃሴ እንዲቆም ጥሪ አቅርበዋል ። ኔታንያሁ ሀማስ እስኪጠፋ ድረስ ጦርነቱን እንደሚቀጥል ገልፀው ታጋቾቹን ወደ ቤት ለማምጣት ወታደራዊ ግፊት እንደሚያስፈልግ ተናግረዋል (AP)።  
    AMHARIC.VOANEWS.COM
    እስራኤላዊ - አሜሪካዊው ኸርሽ ጎልድበርግ-ፖሊን ጨምሮ እስራኤል በጋዛ ውስጥ የ6 ታጋቾችን አስከሬን ማግኘቷ ተገለፀ።
    እስራኤል የ6 ታጋቾችን አስክሬን ጋዛ ውስጥ ማግኘቷን በዛሬው ዕለት አስታወቀች። ከእነዚህ መካከል በሀማስ ከተያዙ እና በእጅጉ ታዋቂ ከነበሩት መካከል አንዱ የነበረው ወጣቱ እስራኤላዊ-አሜሪካዊ ኸርሽ ጎልድበርግ- ፖሊን ይገኝበታል ።ከዓለም መሪዎች ጋር የተገናኙት ወላጆቹ ነጻ እንዲወጣ ግፊት ሲያደርጉ ቆይተዋል ። የእስራኤል ጦር በስፍራው ከመድረሱ ጥቂት ቀደም ብሎ ስድስቱም ታጋቾች መገደላቸውን አስታውቋል። የታጋቾቹ አስክሬን መገኘት ፣ ብዙ እስራኤላውያን ለ10...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    የኢራኑን ፕሬዚደንት የገደለው የሂሊኮፕተር አደጋ መንስኤ አስቸጋሪ አየር ሁኔታ መሆኑን የመጨረሻው ምርመራ ይፋ አደረገ
    የቀድሞው ኢራን ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ የተገደሉበት የሄሊኮፕተር አደጋ በዋነኛነት የተከሰተው ከባድ ጭጋግ በታከለበት (አስቸጋሪ) የአየር ሁኔታ ምክንያት መሆኑን ፣ የመጨረሻ ምርመራ ውጤቶችን ዋቢ ያደረገው የኢራን መንግስት ቴሌቭዥን በዛሬው እለት ዘግቧል። የሀገሪቱ መንፈሳዊ መሪ አያቶላህ አሊ ካሜኔ ተተኪ ሊሆኑ ይችላሉ በሚል ሲታዩ የከረሙት ወግ አጥባቂው ፕሬዝዳንት ኢብራሂም ራይሲ ፣ በግንቦት ወር በአዘርባጃን ድንበር አቅራቢያ በሚገኝ ተራራማ አካባቢ ነበር...
    0 Comments 0 Shares
  • AMHARIC.VOANEWS.COM
    ሞስኮ ኪየቭን በከፍተኛ የሰው አልባ አውሮፕላን ጥቃት ከሰሰች
    የሩስያ ባለስልጣናት ዩክሬን እሁድ ማለዳ ላይ በሞስኮ እና በቴቨር ክልሎች የኃይል እና የነዳጅ ማጣሪያ ፋብሪካዎችን ጨምሮ በበርካታ የሀገሪቱ ክልሎች ላይ ያነጣጠረ የሰው አልባ አውሮፕላኖችን ጥቃት ማድረሷን ገለጹ ። በመንግስት የሚተዳደረው ታስ የዜና ወኪል ፣ የሩስያ መከላከያ ሚኒስቴርን ጠቅሶ እንደዘገበው ፣ የሀገሪቱ የአየር መከላከያ አውታሮች 158 ሰው አልባ አውሮፕላኖችን አውድመዋል። ሚኒስቴሩ በቴሌግራም እንዳስታወቀው ከዩክሬን ጋር በሚያዋስኑት የኩርስክ፣...
    0 Comments 0 Shares
  • ካሲናዬ አዲስ ፊልም (Kassinaye) New ethiopian movie 2024 Maya Media Presents |
    ካሲናዬ አዲስ ፊልም (Kassinaye) New ethiopian movie 2024 Maya Media Presents |
    0 Comments 0 Shares
  • ከmedicine dropout እስከ Amazon Gugut podcast EP#163
    ከmedicine dropout እስከ Amazon Gugut podcast EP#163
    0 Comments 0 Shares
  • በአድናቂዎቹ ጥያቄ አሜሪካ ዲሲ ያላችሁ ለተወዳጁ ሮፍናን ኮንሰርት ዝግጁ??
    በአድናቂዎቹ ጥያቄ አሜሪካ ዲሲ ያላችሁ ለተወዳጁ ሮፍናን ኮንሰርት ዝግጁ??
    0 Comments 0 Shares
  • ሰይፉ ከአሜሪካ መልስ … የፅድቅ መንገድ #seifufantahun #seifuonebs
    ሰይፉ ከአሜሪካ መልስ … የፅድቅ መንገድ #seifufantahun #seifuonebs
    0 Comments 0 Shares
  • ከትውልደ ኢትዮጽያዊያን በሀብት 1ኛው ቱጃር ...ብዙም ቃለምልልስ አልወድም...ለ 5 ሺ ሰዎች በአሜሪካ ስራ የፈጠሩ ... ጆ ማሞ ካቻ #seifuonebs
    ከትውልደ ኢትዮጽያዊያን በሀብት 1ኛው ቱጃር ...ብዙም ቃለምልልስ አልወድም...ለ 5 ሺ ሰዎች በአሜሪካ ስራ የፈጠሩ ... ጆ ማሞ ካቻ #seifuonebs
    0 Comments 0 Shares