• U.S.Embassy Addis Ababa:
    The U.S. Embassy Addis Ababa website has a new look! We invite you to visit our new website for information about the Embassy, bilateral relations, visas, business and educational opportunities, and many more. The new website is easier to navigate and will work better on mobile devices. Visit our new website and let us know what you think about it.
    https://et.usembassy.gov/
    U.S.Embassy Addis Ababa: The U.S. Embassy Addis Ababa website has a new look! We invite you to visit our new website for information about the Embassy, bilateral relations, visas, business and educational opportunities, and many more. The new website is easier to navigate and will work better on mobile devices. Visit our new website and let us know what you think about it. https://et.usembassy.gov/
    0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • 0 Comments 0 Shares
  • ከ2007 ዓ.ም. መገባደጃ ጀምሮ በቅርቡ እንደየአከፋፈላቸው ይተላለፋሉ እየባለ ላለፉት ሦስት ዓመታት ተመዝጋቢውን ግራ ሲያጋቡ ከነበሩት የክራውንና ሠንጋ ተራ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሠንጋ ተራዎችን ሙሉ በሙሉ መረከቡ ታወቀ፡፡

    በአምስት ብሎኮች የተገነቡ በእያንዳንዱ ብሎክ 60፣ በድምሩ 300 ቤቶች የግንባታው ባለቤት ከሆነው የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ ጋር በመነጋገርና አንዳንድ ያልተጠናቀቁ ነገሮችን ለማጠናቀቅ በመፈራረም መረከቡን፣ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ ኃላፊ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡

    ኢንተርፕራይዙ በክራውን ሳይት ካሉት 14 ብሎኮች ውስጥ ሰባቱን ማስረከቡን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ የክራውን ሳይት እያንዳንዱ ብሎክ 48 ቤቶችን እንደያዙ የገለጹት ኃላፊው፣ በድምሩ 336 ቤቶችን በተመሳሳይ ሁኔታ ማስረከቡን አስረድተዋል፡፡ ኢንተርፕራይዙ ያጠናቀቃቸውን ብሎኮች በየቀኑ እያስረከበ መሆኑን ጠቁመው፣ ሙሉ በሙሉ አስረክቦ የሚጨርስበትን ቀን መገመት ባይቻልም በቅርቡ ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡

    ምናልባት በሰኔ ወር መጨረሻ ወይም በሐምሌ ወር መጀመሪያ አካባቢ ለተመዝጋቢዎች ይተላለፋሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ግምታቸውን የተናገሩት ኃላፊው፣ በሁለቱም ሳይቶች ያሉት በድምሩ 972 ቤቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በሠንጋ ተራና በክራውን ሳይቶች በአጠቃላይ 1,292 መኖሪያ ቤቶች እንደሚተላለፉ ሲነገር ቆይቶ እንዴት 972 ብቻ ይሆናሉ የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ኃላፊው፣ በሁለቱም ሳይቶች የሚገኙ 320 የንግድ ቤቶች በመሆናቸው ባንኩ እንደማይመለከተው ገልጸዋል፡፡

    በ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጠቅላላ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ከ164 ሺሕ በላይ ቢሆንም፣ 150 ሺሕ ያህሉ ሳያቋርጡ እየቆጠቡ መሆናቸው ታውቋል፡፡፡ ከ16,000 በላይ የሚሆኑት መቶ በመቶ የከፈሉ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ከ60 በመቶ በላይ የቆጠቡ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ 39,229 የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውም ተገልጿል፡፡ ግንባታቸው የተጠናቀቀው ሁለቱ ሳይቶች (972 ቤቶች) ለተመዘጋቢዎቹ ማለትም ቀደም ብለው መቶ በመቶ ለከፈሉት 2,200 ተመዝጋቢዎች (የኢንተርፕራይዙ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለመገናኛ ብዙኃን በገለጹት መሠረት) መቼ እንደሚተላለፉ አልታወቀም፡፡
    ከ2007 ዓ.ም. መገባደጃ ጀምሮ በቅርቡ እንደየአከፋፈላቸው ይተላለፋሉ እየባለ ላለፉት ሦስት ዓመታት ተመዝጋቢውን ግራ ሲያጋቡ ከነበሩት የክራውንና ሠንጋ ተራ የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ውስጥ፣ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ የሠንጋ ተራዎችን ሙሉ በሙሉ መረከቡ ታወቀ፡፡ በአምስት ብሎኮች የተገነቡ በእያንዳንዱ ብሎክ 60፣ በድምሩ 300 ቤቶች የግንባታው ባለቤት ከሆነው የቁጠባ ቤቶች ልማት ኢንተርፕራይዝ ጋር በመነጋገርና አንዳንድ ያልተጠናቀቁ ነገሮችን ለማጠናቀቅ በመፈራረም መረከቡን፣ ስማቸው እንዲገለጽ ያልፈለጉ የኢትዮጵያ ንግድ ባንክ ከፍተኛ ኃላፊ ለሪፖርተር ተናግረዋል፡፡ ኢንተርፕራይዙ በክራውን ሳይት ካሉት 14 ብሎኮች ውስጥ ሰባቱን ማስረከቡን ኃላፊው ገልጸዋል፡፡ የክራውን ሳይት እያንዳንዱ ብሎክ 48 ቤቶችን እንደያዙ የገለጹት ኃላፊው፣ በድምሩ 336 ቤቶችን በተመሳሳይ ሁኔታ ማስረከቡን አስረድተዋል፡፡ ኢንተርፕራይዙ ያጠናቀቃቸውን ብሎኮች በየቀኑ እያስረከበ መሆኑን ጠቁመው፣ ሙሉ በሙሉ አስረክቦ የሚጨርስበትን ቀን መገመት ባይቻልም በቅርቡ ይጠናቀቃል የሚል እምነት እንዳላቸው ጠቁመዋል፡፡ ምናልባት በሰኔ ወር መጨረሻ ወይም በሐምሌ ወር መጀመሪያ አካባቢ ለተመዝጋቢዎች ይተላለፋሉ የሚል እምነት እንዳላቸው ግምታቸውን የተናገሩት ኃላፊው፣ በሁለቱም ሳይቶች ያሉት በድምሩ 972 ቤቶች መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ በሠንጋ ተራና በክራውን ሳይቶች በአጠቃላይ 1,292 መኖሪያ ቤቶች እንደሚተላለፉ ሲነገር ቆይቶ እንዴት 972 ብቻ ይሆናሉ የሚል ጥያቄ የቀረበላቸው ኃላፊው፣ በሁለቱም ሳይቶች የሚገኙ 320 የንግድ ቤቶች በመሆናቸው ባንኩ እንደማይመለከተው ገልጸዋል፡፡ በ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች ጠቅላላ ተመዝጋቢዎች ቁጥር ከ164 ሺሕ በላይ ቢሆንም፣ 150 ሺሕ ያህሉ ሳያቋርጡ እየቆጠቡ መሆናቸው ታውቋል፡፡፡ ከ16,000 በላይ የሚሆኑት መቶ በመቶ የከፈሉ ሲሆን፣ ቀሪዎቹ ከ60 በመቶ በላይ የቆጠቡ መሆኑም ተጠቁሟል፡፡ 39,229 የ40/60 የጋራ መኖሪያ ቤቶች በግንባታ ላይ መሆናቸውም ተገልጿል፡፡ ግንባታቸው የተጠናቀቀው ሁለቱ ሳይቶች (972 ቤቶች) ለተመዘጋቢዎቹ ማለትም ቀደም ብለው መቶ በመቶ ለከፈሉት 2,200 ተመዝጋቢዎች (የኢንተርፕራይዙ የሕዝብ ግንኙነት ኃላፊ ለመገናኛ ብዙኃን በገለጹት መሠረት) መቼ እንደሚተላለፉ አልታወቀም፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዳማ ቅርንጫፍ ስሚንቶ በጫነ ተሽከርካሪ ተደብቆ ሊያልፍ የነበረ 215 ሺህ ብር ግምት ያለው ሺሻ መያዙን አስታወቀ።

    የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ የህግ ማስከበር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ለታ ለኢዜአ እንደገለፁት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-45423 አ.አ በሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ከላይ ለሽፋን ከጫነው 40 ከረጢት ሲሚንቶ ስር ደብቆ ሊያሳልፍ የነበረው 2 ሺህ 156 ስቴካ ሺሻ ተይዟል።

    የተያዘውም ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ መሰረት ሽሻውን የጫነው ተሽከርካሪ ከትናንት በስቲያ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት አዳማ ከተማ ውሰጥ በጉምሩክ ሰራተኞችና በፌደራል ፖሊስ አባላት አማካኝነት ነው።

    በወቅቱ አሽከርካሪው ከቆመበት ስፍራ መኪናውን አስነስቶ በፍጥነት ለማመለጥ በመሞከሩ የተሽከርካሪውን ጎማ ለመመታት በተተኮሰ ጥይት ግራ ጎኑን ተመቶ በአዳማ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን አስተባባሪው ተናግረዋል።

    በተመሳሳይም በአዳማና ቢሾፍቱ ከተሞች ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ 673 ሺህ 303 ብር ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ መያዙንም አመልክተዋል።

    ከተያዙት መካከል ልባሽና አዳዲስ ጨርቆች ፣ አሮጌ ጫማዎች ፣ የምግብ ዘይት ፣ ሽቶና ማስዋቢያዎች ይገኙበታል ።

    የኮንትሮባንድ ዕቃው በቁጥጥር ስር የዋለው በህብረተሰቡ፣በፀጥታ ሃይሎችና በመስተዳድር አካላት የተቀናጀ ጥረት ነው።

    ለህዝብ ጤናና ለአገር ኢኮኖሚ ስጋት እየሆነ የመጣውን የኮንተሮ ባንድ እንቅሰቃሴ ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህብረተሰብ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስተባባሪው ጠይቀዋል::-ኢዚአ
    በኢትዮጵያ ገቢዎችና ጉምሩክ ባለስልጣን የአዳማ ቅርንጫፍ ስሚንቶ በጫነ ተሽከርካሪ ተደብቆ ሊያልፍ የነበረ 215 ሺህ ብር ግምት ያለው ሺሻ መያዙን አስታወቀ። የቅርንጫፍ ፅህፈት ቤቱ የህግ ማስከበር የስራ ሂደት አስተባባሪ አቶ ብርሃኑ ለታ ለኢዜአ እንደገለፁት የሰሌዳ ቁጥሩ ኮድ 3-45423 አ.አ በሆነ አይሱዙ የጭነት መኪና ከላይ ለሽፋን ከጫነው 40 ከረጢት ሲሚንቶ ስር ደብቆ ሊያሳልፍ የነበረው 2 ሺህ 156 ስቴካ ሺሻ ተይዟል። የተያዘውም ህብረተሰቡ በሰጠው ጥቆማ መሰረት ሽሻውን የጫነው ተሽከርካሪ ከትናንት በስቲያ ከሌሊቱ ዘጠኝ ሰዓት አዳማ ከተማ ውሰጥ በጉምሩክ ሰራተኞችና በፌደራል ፖሊስ አባላት አማካኝነት ነው። በወቅቱ አሽከርካሪው ከቆመበት ስፍራ መኪናውን አስነስቶ በፍጥነት ለማመለጥ በመሞከሩ የተሽከርካሪውን ጎማ ለመመታት በተተኮሰ ጥይት ግራ ጎኑን ተመቶ በአዳማ ሆስፒታል የህክምና እርዳታ እየተደረገለት መሆኑን አስተባባሪው ተናግረዋል። በተመሳሳይም በአዳማና ቢሾፍቱ ከተሞች ባለፉት አምስት ቀናት ውስጥ 673 ሺህ 303 ብር ግምት ያለው የኮንትሮባንድ ዕቃ መያዙንም አመልክተዋል። ከተያዙት መካከል ልባሽና አዳዲስ ጨርቆች ፣ አሮጌ ጫማዎች ፣ የምግብ ዘይት ፣ ሽቶና ማስዋቢያዎች ይገኙበታል ። የኮንትሮባንድ ዕቃው በቁጥጥር ስር የዋለው በህብረተሰቡ፣በፀጥታ ሃይሎችና በመስተዳድር አካላት የተቀናጀ ጥረት ነው። ለህዝብ ጤናና ለአገር ኢኮኖሚ ስጋት እየሆነ የመጣውን የኮንተሮ ባንድ እንቅሰቃሴ ለመግታት በሚደረገው ጥረት የህብረተሰብ ተሳትፎ ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበትም አስተባባሪው ጠይቀዋል::-ኢዚአ
    0 Comments 0 Shares
  • አልቫሮ ሞራታ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ በ73 ሚሊየን ፓውንድ ለመዘዋወር ከስምምነት ላይ መደረሱ

    ታውቋል፡፡ሰኞ ላይ ይፈርማል የተባለው ኮንትራት እስከ 2022 በኦልድትራፎርድ የሚቆየው ነው የተባለው፡፡

    ሪያል ማድሪድ ከዚህ በፊት ዩናይትድ ያቀረበውን የ53 ሚሊየንፓውንድ የግዢ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡

    ዝላታን ኢብርሃሞቪችን በሚቀጥለው ዓመት የሚያጡት ጆሴ ሞሪንሆ የሞራታ ወደ ክለቡ መምጣት

    ቡድኑን ሊፈጠርበት የሚችለውን ክፍተት ይሞላላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡አልቫሮ ሞራታ ከሪያል ማድሪድ

    ጋር የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወቃል፡፡
    አልቫሮ ሞራታ ወደ ማንቸስተር ዩናይትድ በ73 ሚሊየን ፓውንድ ለመዘዋወር ከስምምነት ላይ መደረሱ ታውቋል፡፡ሰኞ ላይ ይፈርማል የተባለው ኮንትራት እስከ 2022 በኦልድትራፎርድ የሚቆየው ነው የተባለው፡፡ ሪያል ማድሪድ ከዚህ በፊት ዩናይትድ ያቀረበውን የ53 ሚሊየንፓውንድ የግዢ ጥያቄ ውድቅ ማድረጉ ይታወሳል፡፡ ዝላታን ኢብርሃሞቪችን በሚቀጥለው ዓመት የሚያጡት ጆሴ ሞሪንሆ የሞራታ ወደ ክለቡ መምጣት ቡድኑን ሊፈጠርበት የሚችለውን ክፍተት ይሞላላቸዋል ተብሎ ይጠበቃል፡፡አልቫሮ ሞራታ ከሪያል ማድሪድ ጋር የቻምፒዮንስ ሊጉን ዋንጫ ማንሳቱ ይታወቃል፡፡
    0 Comments 0 Shares
  • ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታውን ከጋና ብሄራዊ ቡድን ጋር የሚያደርገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ማለዳ ወደ አክራ አቅንቷል።

    ዋልያዎቹ ቀድሞ በተያዘላቸው ሆቴል የአየር ሚዛን መጠበቂያው (ኤር ኮንድሽነር) የማይሰራ በመሆኑ በዚያ ለማረፍ ፈቃደኛ ሳሆኑ ቀርተዋል ተብሎ የተዘገበ ሲሆን ከሰዓታት መጉላላት በኋላ ሌላ ተለዋጭ ሆቴል ላይ እንዲያርፉ ተደርጓልም ተብሏል፡፡

    የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ተጫዋቾችን በማሰባሰብ ለጨዋታው ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል።

    አሰልጣኙ ለጋናው ጨዋታ የመረጧቸውን የመጨረሻ 22 ተጨዋቾችም ይፋ አድርገዋል።

    ብሄራዊ ቡድኑ አክራ ከገባ በኋላ በነገው እለት ጨዋታውን ወደሚያደርግበት ኩማሲ የሚያቀና ይሆናል።

    ለጨዋታው የተመረጡ ተጫዋቾች

    ግብ ጠባቂዎች፦

    ጀማል ጣሰው /ጅማ አባ ቡና)

    ለአለም ብርሃኑ /ሲዳማ ቡና/

    አቤል ማሞ /መከላከያ/

    ተከላካዮች፦

    አስቻለው ታመነ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/

    ሳልሃዲን ባርጌቾ/ቅዱስ ጊዮርጊስ/

    ሙጂብ ቃሲም /አዳማ ከነማ/

    ስዩም ተስፋዬ /ደደቢት/

    አንተነህ ተስፋዬ /ሲዳማ ቡና/

    አዲሱ ተስፋዬ /መከላከያ/

    አብዱልከሪም መሀመድ /ኢትዮጵያ ቡና/

    ተስፋዬ በቀለ /አዳማ ከነማ/

    አማካዮች፦

    ሽመልስ በቀለ /ፔትሮጄት/

    ብሩክ ቃልቦሬ /አዳማ ከነማ/

    ጋዲሳ መብራቴ /ሀዋሳ ከነማ/

    ሽመክት ጉግሳ /ደደቢት/

    ጋቶች ፓኖም /ኢትዮጵያ ቡና/

    ሙሉአለም መስፍን /ሲዳማ ቡና/

    አጥቂዎች፦

    ሳልሃዲን ሰኢድ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/

    ኡመድ ኡኩሪ /ኤንታግ አልሀርቢ/
    ጌታነህ ከበደ (ደደቢት)

    አብዱራህማን ሙባረክ /ፋሲል ከነማ/

    አዲስ ግደይ /ሲዳማ ቡና/

    የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከጋና፣ ሴራሊዮን እና ኬንያ ጋር መደልደሉ ይታወሳል – Ethio news

    FBC
    ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ የማጣሪያ ጨዋታውን ከጋና ብሄራዊ ቡድን ጋር የሚያደርገው የኢትዮጵያ ብሄራዊ ቡድን ዛሬ ማለዳ ወደ አክራ አቅንቷል። ዋልያዎቹ ቀድሞ በተያዘላቸው ሆቴል የአየር ሚዛን መጠበቂያው (ኤር ኮንድሽነር) የማይሰራ በመሆኑ በዚያ ለማረፍ ፈቃደኛ ሳሆኑ ቀርተዋል ተብሎ የተዘገበ ሲሆን ከሰዓታት መጉላላት በኋላ ሌላ ተለዋጭ ሆቴል ላይ እንዲያርፉ ተደርጓልም ተብሏል፡፡ የብሄራዊ ቡድኑ አሰልጣኝ አሸናፊ በቀለ ተጫዋቾችን በማሰባሰብ ለጨዋታው ዝግጅታቸውን ሲያደርጉ ቆይተዋል። አሰልጣኙ ለጋናው ጨዋታ የመረጧቸውን የመጨረሻ 22 ተጨዋቾችም ይፋ አድርገዋል። ብሄራዊ ቡድኑ አክራ ከገባ በኋላ በነገው እለት ጨዋታውን ወደሚያደርግበት ኩማሲ የሚያቀና ይሆናል። ለጨዋታው የተመረጡ ተጫዋቾች ግብ ጠባቂዎች፦ ጀማል ጣሰው /ጅማ አባ ቡና) ለአለም ብርሃኑ /ሲዳማ ቡና/ አቤል ማሞ /መከላከያ/ ተከላካዮች፦ አስቻለው ታመነ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/ ሳልሃዲን ባርጌቾ/ቅዱስ ጊዮርጊስ/ ሙጂብ ቃሲም /አዳማ ከነማ/ ስዩም ተስፋዬ /ደደቢት/ አንተነህ ተስፋዬ /ሲዳማ ቡና/ አዲሱ ተስፋዬ /መከላከያ/ አብዱልከሪም መሀመድ /ኢትዮጵያ ቡና/ ተስፋዬ በቀለ /አዳማ ከነማ/ አማካዮች፦ ሽመልስ በቀለ /ፔትሮጄት/ ብሩክ ቃልቦሬ /አዳማ ከነማ/ ጋዲሳ መብራቴ /ሀዋሳ ከነማ/ ሽመክት ጉግሳ /ደደቢት/ ጋቶች ፓኖም /ኢትዮጵያ ቡና/ ሙሉአለም መስፍን /ሲዳማ ቡና/ አጥቂዎች፦ ሳልሃዲን ሰኢድ /ቅዱስ ጊዮርጊስ/ ኡመድ ኡኩሪ /ኤንታግ አልሀርቢ/ ጌታነህ ከበደ (ደደቢት) አብዱራህማን ሙባረክ /ፋሲል ከነማ/ አዲስ ግደይ /ሲዳማ ቡና/ የኢትዮጵያ ብሔራዊ ቡድን ለ2019 የአፍሪካ ዋንጫ ማጣሪያ ከጋና፣ ሴራሊዮን እና ኬንያ ጋር መደልደሉ ይታወሳል – Ethio news FBC
    0 Comments 0 Shares