ማበድ ደጉ!

0
0

«ዘውድአለም ታደሰ»

ዳኒ የሰፈራችን ፅድት ያለ እብድ ነው። ቤተሰቦቹ ሃብታሞች ስለሆኑ ምንም ነገር አይቸግረውም። ልብሱም ንፁህ ነው። ያው አልፎ አልፎ የሚሰጠው የኪስ ገንዘብ ካልበቃው የሚግባባውን ሰው መጠየቁ አይቀርም። የሰፈሩም ሰው ስለሚወደው አይጨክንበትም። 
ከዚህ በተረፈ ግን ዳኒ ጀንተል ያለ እብድ ነው። ለምን እንዳበደ ለምን እውቅ ሃኪሞች ጋር ሄዶ ሊፈወስ እንዳልቻለ የሚያውቅ የለም። ዛሬ ሰብሰብ ብለን ቡና የምንጠጣባት ቤት ቁጭ ብለን ነበር። ዳኒም ፈንጠር ብሎ በሩ ጋር ተቀምጧል። ድንገት ዳኒን የማያውቅ አንድ ነጭናጫ ሰውዬ መጥቶ አጠገቡ ተቀመጠና ቡና አዘዘ። ዳኒ የሆነ ነገር እንደሚለው ገምቼ የሚያወሩትን መከታተል ጀመርኩ ...

ዳኒ ሰውየውን ዞር ብሎ በጥርጣሬ ገላመጠው። ሰውየውም መልሶ ገላመጠው። ዳኒ ፈራ መሰለኝ ዞሮ ፈገግ አለ። ሰውዬውም ፈገግ አለና ጨዋታ ለመጀመር ያህል «ዘንድሮ በቃ ቤት ኪራይ ጣራ ነካ አይደል?» አለው።
ዳኒ አንገቱን ነቅንቆ «ነካ? ዘንድሮ ምን አናጢ አለ? ሁሉም ወንበዴ ሆኗልኮ» አለው። 
ሰውየው ግራ ተጋብቶ «የምን አናጢ?» ሲለው ዳኒ ኮስተር ብሎ
«አናጢ አታውቅም? እነዚህ መዶሻ ይዘው ሚዞሩት ናቸዋ! ጣሪያውን ዝቅ አርገው ስለሚሰሩት እኮ ነው ኪራዩ ጣሪያ የነካው» ሲለው ሰውየው የብስጭት ሳቅ ስቆ
«አንተ ኮንዶሚኒየም ደርሶሃል መሰለኝ ትቀልዳለህ» አለው። ዳኒ ቡናውን ፉት ብሎ ዝም አለ።

ሰውየው ግን ዝም አላለም። «ኑሮ ተወዷል። ሁሉ ነገር እያሻቀበ ነው። አዲሳባ ላይ መኖር አልተቻለም» ሲለው ዳኒ አሁንም ቡናውን ፉት ብሎ
«ታዲያ መኖር ካልቻልክ እንዴት ኖርክ?» አለው።
«ሰውዬ አረ ቀልዱን አቁም። ልማታዊ ባለሃብት ነህ እንዴ?» አለው ከልቡ ተበሳጭቶ
«አዎ! ሃብታም ነኝ መሰለኝ።» አለ ዳኒ
«አረ ....ለዛ ነዋ። ለመሆኑ ምን እየሰራህ ነው?»
«አሁን?»
«አዎ»
«አሁን?»
«አዎ»
«ቡና እየጣሁ ነዋ»

ሰውየው በዳኒ ሁኔታ ግራ ተጋብቶ። «አይ ለመኖር ምን እየሰራህ ነው ማለቴ ነው?»
«ለመኖርማ እተነፍሳለሁ። እቅማለሁ። ቡና እጠጣለሁ»
«አይ ጥሩ ነው።» አለ ሰውዬው። 
ጥቂት ፀጥታ ሰፈነ። ሰውየውም የቀረበለትን ቡና ፉት ብሎ ዳኒን በቆረጣ ይገረምመው ጀመር።

«አንተስ ለመኖር ምን ትሰራለህ?» አለው ዳኒ
«ጉምሩክ ነው ምሰራው?»
«ኦህ ጥሩ ስራ ነው። የራስህን ከፍተህ ነው?» ሲለው ሰውየው ትን እስኪለው ስቆ «አረ ተቀጥሬ ነው»
«ደሞዝህ ስንት ነው?»
«አራት ሺ ብር»
«በቀን ነው?»
«ሃሃሃሃ አረ በወር ነው» 
«በወር ስንት ቀን?» 
ሰውየው በዳኒ ጥያቄ ተገርሞ «በወር አንድ ቀን ነዋ» 
«ታዲያ በወር አንድ ቀን ከተከፈለህ ለምንድነው ሰላሳ ቀን ምትሰራው?»

ሰውየው አሁን ትእግስቱን መቆጣጠር አልቻለም። «ሰውዬ በድህነቴ ለምን ታላግጣለህ? ደሃ ዘመድ የለህም እንዴ?» ሲለው ዳኒ ደንገጥ ብሎ
«አረ አለኝ። አክስቴ ደሃ ነች። ሁሌም ብር ስጪኝ ስላት የለኝም ነው ምትለኝ» አለው። 
«አንተ እንዴት በዚህ እድሜህ ካክስትህ ብር ትጠይቃለህ?» ሲለው ዳኒ ፈጠን ብሎ «አይ እሷን ብቻ አይደለም ምጠይቀው። ሁሉንም ነው ምጠይቀው»
«ለምንድን ነው ሰውን ገንዘብ ምትጠይቀው?»
«እና ከሰው ሌላ ማንን ልጠይቅ?»
«አይ ሰውን ገንዘብ ከመለመን እግዜርን መለመን ይሻላል»
«እግዜር ብዙ ጠያቂ አለው። ላለማስቸገር ነው» ብሎ ቡናውን ፉት አርጎ አስቀመጠ።

ሰውየው ከኪሱ የቡናውን ሂሳብ እያወጣ «ለማንኛውም ስለተዋወቅን ደስ ብሎኛል» አለው ወደዳኒ ዞሮ
«መቼ ተዋወቅን?» አለ ዳኒ
«ውይ ለካ አልተዋወቅንም ሃብታሙ እባላለሁ» ብሎ እጁን ዘረጋ
«በወር አንድ ቀን እየተከፈለህ ሃብታሙ?» አለና ጨበጠው። 
«እንገናኛለን» አለ ሰውዬው እየተነሳ
«የት?» አለ ዳኒ
ሰውየው ፈገግ ብሎ «እዚሁ ነዋ»
«መች?»
«ነገ መምጣቴ አይቀርም»
«ስንት ሰአት?»
ሰውየው ግራ ተጋብቶ «ልክ በዚህ ሰአት» 
«አሁን ስንት ሰአት ነው?» አለ ዳኒ
«አሁን ሰባት ተኩል ነው» 
«አይ ሰባት ተኩል አይመቸኝም» 

ፍለጋ
Categories
Read More
Uncategorized
አንዳንድ ነገሮች ስለ ግማደ መስቀሉ
(ዳንኤል ክብረት) ስለ ግማደ መስቀሉ አመጣጥ ግሼን በሚገኘው በመጽሐፈ ጤፉት የተጻፈውን ባለፉት ዘመናት ስናነበውና ስንሰማው ኖረናል፡፡ እስኪ ዛሬ ደግሞ...
By Binid Dre 2017-11-25 13:26:59 0 0
Uncategorized
‹‹ስጋን ማመን አርዶ ነው!››
‹‹ስጋን ማመን አርዶ ነው!››(አሳዬ ደርቤ)‹‹ምሳዬን የት...
By Assaye Derbie 2017-11-12 07:31:32 0 0
Shopping
Can Minidumperfactory Electric Garden Loader Manage Materials Across Garden Sites
Electric Garden Loader usage has become increasingly common in daily garden work as landscaping...
By Minidumperfactory Minidumperfactory 2025-12-18 07:00:40 0 0
Uncategorized
70 ሜትር ከፍታ ባለው ገመድ ላይ የተራመደው ግለሰብ አዲስ ክብረ ወሰን ይዟል
ከመሬት230 ጫማ ወይም 70 ሜትር ከፍታ ላይ በታሰረ ቀጭን ገመድ ላይ የተራመደው ግለሰብ አዲስ የዓለም ክብረ ወሰን ይዟል። ናታን ፓውሊን የተባለው...
By Dagmawisol 2017-12-15 06:18:58 0 0
Uncategorized
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)
የአራዶች ወግ (ክፍል አንድ…..)(ማስጠንቀቂያ….ይህ ጽሁፍ ልክ እንደ እሁድ ረዥም ስለሆነ ስራ ያለበት ሰው ከእሁድ ውጪ...
By Andualem Buketo 2017-11-12 15:13:23 0 0