ሁለቱ ወንድማማቾች ___

0
0

 በአንድ የገጠር መንደር በቤተሰቦቻቸው የእርሻ ማሳ በጋራ እያመረቱ የሚተዳደሩ ሁለት ወንድማማቾች ነበሩ፡፡ አንደኛው ትዳር መስርቶ ብዙ ቤተሰብ የሚያስተዳደር ሲሆን አንደኛው ግን ገና አላገባም ብቻውን ነው የሚኖር፡፡ በምርት መሰብሰቢያ ወቅት ያገኙትን ምርት እኩል ይካፈሉ ነበር፡፡ ታዲያ አንድ ቀን ትዳር ያልመሰረተው ለእራሱ እንዲህ አለ፡፡ “ያገኘነውን ምርት እኩል መካፈል ፍተሃዊ አይደለም፡፡ እኔ ብቻየን ስለሆንኩ ትንሽ ነገር ነው ሊበቃኝ የሚችለው፡፡” እንዲህ ብሎ መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግነ አድርጎ ከጎተራው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬ እያነሳ በቤታቸው መካከል ባለው መስክ አቋርጦ ከወንድሙ ጎተራ ይሞላለት ነበር፡፡ በተመሳመሳይ ሁኔታ ትዳር የመሰረተው ወንድሙም ለእራሱ እንዲህ ይላል “ምርታችንን እኩል መካፈላችን ትክክል አይደለም፡፡ ሁኖ ሁኖ እኔ ባለ ትዳር ነኝ በመጭዎቹ አመታት አንዳች ነገር ቢፈጠር እንኳን ልጆቼና ሚስቴ ይንከባከቡኛል፡፡ ይሄ ወንድሜ ግን ብቻውን ነው፡፡ ማንም የሚንከባከበው የለውም ስለሆነም” አለና መሸት ሲልለት ጨለማውን ተግነ አድርጎ ኬሻ ሙሉ ጥራ ጥሬ እየወሰደ ከላጤ ወንድሙ ጎተራ ይጨምራል፡፡ እንዲህ እንዲህ እያሉ ዓመቱ ተጋመሰ የእህል ጎተራቸው ያልቀነሰበት ምክንያት ግን እንቆቅልሽ ሆኖባቸዋል፡፡ ከዛም አንድ ቀን ምሽት ሁለቱም እንደልማዳቸው አንደኛው ላንደኛው ኬሻ ሙሉ ጥራጥሬውን ይዘው ሲተላለፉ ሁኔታዎች ተገጣጠሙና መንገድ ላይ ተጋጩ፡፡ ቀስ አድርገው ሸክማቻን አውርደው ሲተያዩ ወደንድማማቾቹ ነበሩ፡፡ በልባዊ ፍቅር ተቃቀፉ፡፡ ፊት ለፊት ተነጋግረው የበለጠውን አንደኛው መውሰድ እንዲችል ማድረግ ጠፍቷቸው አይደለም ግን አንተ ትብስ አንተ ትብስ እየተባባሉ ውሳኔ ላይ መድረስ እንደማይችሉ ስላወቁ የፈጠሩት መላ ይመስላል፡፡ እንኳንስ ስጡ ሳይባሉ ለመስጠት መፍቀድ ቀርቶ ቢጠየቁ እንኳ እኩል ድርሻየ ነው ማለት በሚቻልበት ሁኔታ የበለጠውን ለመስጠት መሻት ከልባዊ ፍቀር ውጭ ሊመጣ አይችልም፡፡ ለሰጨውም ሆነ ለተቀባዩ ሳይቀንስ የሚሰጥ ስጦታ ልባዊ ፍቅር ብቻ ነው፡፡ እንዲህ አይነታ ፍቀር ይስጠን ነው የሚባለው፡፡ ምንጭ፡ Story of Two Brothers (#ምስጋናው ግሸን ወልደ አገሬ) 17-09-2007 ዓ.ም

Like
1
Search
Categories
Read More
Uncategorized
Selling
Product
By Hana 2017-11-25 17:05:20 0 0
Uncategorized
_ከምድር ሁሉ ሃብታሙ ስፍራ……..መቃብር
__ከምድር ሁሉ ሃብታሙ ስፍራ……..መቃብር “The graveyard is the richest place on earth,...
By Seller 2017-12-01 08:05:09 0 0
Other
MINI: Xe Nâng Điện UNICARRIERS J1B1L09 (FB9) 900Kg nhỏ gọn tiện dụng
Bạn đang tìm kiếm một chiếc xe nâng điện mạnh mẽ, linh hoạt và...
By xenangaz 2025-04-16 07:05:21 0 0
Uncategorized
አስገራሚ ቃለ ምልልስ -ሙጋቤ
”መቼም ሙጋቤ መልካም ሰው ነው” ይላል- መንግስቱ ሃይለማርያም የክፉ ቀን ደራሹን ማመስገን ሲጀምር።በርግጥ የሙጋቤን መልካምነት...
By binid 2017-11-26 06:36:34 0 0
Uncategorized
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››
‹‹በህልም የተፈጠረ መወስለት ከሐጢያት ይቆጠር ይሆን?››(አሳዬ ደርቤ)እንዴት ዋላችሁ ምዕመናን? እኔ...
By Assaye 2017-11-12 13:09:47 0 0