አዝናለሁ!

#ETHIOPIA | የራስን ጎጆ ለማሞቅ የጎረቤትን ማቃጠል ወንጀል ነው።

አንድ ሰው ወይንም አንድ ድርጅት ስራ ሲጀምር የሚነድፋቸው እቅዶችና ተግባሮች ይኖሩታል። ለሁሉም እንዳግባቡ የግዜ ሰሌዳም ያበጃል።

ሂደቱን የሚመለከታቸው አካላት ብቻ እንዲያውቁት የሚመረጥ ግዜ አለ። ቅደም ተከተሉን ጠብቆ ወደ ህብረተሰቡ የሚደርስበትም የራሱ ግዜ አለው።

መረጃም ሲሰ'ጥ የመረጃው ልክነትና ልኬት የሚያስጠይቅ ከመሆኑ አንፃር ታስቦ ተመጥኖ መሆን አለበት።

ሁሉም አልቆ ግዜው ሲፈቅድ ብቻ ነው ወደ መግለጫና ወደ ዜና የሚቀርበው።

የዛም ውሳኔ ባለቤት ለፍተው እዛጋ ያደረሱት የኩባንያው ባለቤቶች ብቻ ናቸው። እንደዚህ የሚባል ወሬ አለ እውነት ከሆነ የሚመለከታቸውን ግለሰቦች አነጋግረን አጣርተን እንመጣለን ማለት አንድ ነው።

ባለቤቱ በጉዳዩ ላይ መረጃ መስጠት ካልፈለገና ነገር ግን ጥያቄው ከህዝብ የመጣ ከሆነ መረጃ ሊሰጡን አልቻሉም ተብሎ ማቅረብ የሚቻልበትም ሌላ አግባብ አለ።

ትንሽ ፍንጭ ይዞ ያለግዜው የግምት ዝርዝር ይዞ መቅረብ ያልበሰለ እሸት "ቀጥፎ" ያለግዜው መቅጨት ነውና ሊታሰብበት ይገባል።

ለምሳሌ ከአንድ ሳምንት በፊት ሰይፉ ፋንታሁን ስልክ ደውሎ ቴሌቪዥን ጣቢያ ልትከፍት ነው የሚል ወሬ ሰማሁ እውነት ነወይ ሲል ጠይቆኛል።

ባለቤትነቱ የእኔ ብቻ ያልሆነ በርካታ ህብረተሰቡ የሚወዳቸውና ለሃገራቸው ትልልቅ አስተዋፅዖ ያደረጉ ኢትዮጵያዊያን ባለአክስዮኖችን ጨምሮ በመቋቋም ላይ ያለ የሚዲያ ኩባንያ መሆኑን፤ ብዙ አዳዲስ ነገሮች እንደሚኖረንና በጣም የታሰበበት ከመሆኑ አንፃር ግዜው ሳይደርስ እንዲወራ እንደማንፈልግ ነገር ግን ግዜው ሲደርስ እኔው እንደምደውልለት አደራ ብዬው ስልኩ ተዘጋ።

በሚቀጥለውም ቀን ባልደረባው ታደለ አሰፋ የታደለ ሮባ ሰርግ የእራት ግብዣ ላይ ስራዬ ብሎ መጥቶ ሲጠይቀኝ ይሄን ነገር ማስቆም አለብኝ ብዬ ለሰይፉ እንደነገርኩትና ይበልጥ ለማሳሰብ ብዬ ብዙ ነገር እንደሚያበላሽብን አደራ ጨምሬ ነገርኩት።

አደራ ምንድነው? መረጃውንስ በትክክል ሳይሆን አበላሽቶ ማውራት ምንድነው? በቅርብ ቀን ማለትስ ከየት ያገኛችሁት መረጃ ነው? ስለ ቴሌቪዥን ቻናሎች መብዛት ትችትን ከዚህ ጋር አያይዞስ ማውራት ምንድነው? ከዚህኛው ርዕስ ተነስቶስ ተመሳሳይ ጣቢያ ስፖንሰር የተደረጉበት በሚመስል ሁኔታ በቅርብ እንደሚከፈትና የዚያኛውን ታላቅነትና አስተማማኝነት ስሜታዊ የሆነ ትንታኔ መስጠትስ ምንድነው?

ከዚህ በፊት መግለጫ ልሰጥበት በምፈልገው ትልቅ ጉዳይ ሳነጋግራችሁ ሌላ አካል ፈርታችሁ ከሙያው ስነምግባር ውጪ በመሆን አናቀርብም ብላችሁ አሁን ደግሞ አታቅርቡ ያልኳችሁንስ ማቅረብ ምንድነው? ባለቤትነቱን የኔ ብቻ ማድረጋችሁና በማታውቁት ታሪክ ላይ መሪ ተዋናይ መሆናችሁስ ምንድነው?

ብዙ ነገር ያበላሽብናል ብያችሁ አልነበር?.... ለናንተ ጥሩ ዜና አለኝ... ብዙ ነገር አበላሽቷልና እንኳን ደስ አላችሁ!!

የራስን ጎጆ ለማሞቅ የጎረቤትን ማቃጠል ወንጀል ነው።

የተሰማኝን ሳልደብቅ፣ ሳልቆጥብ መናገሬ የተለመደ ነው ታውቃላችሁ። ከኛ መተቻቸት ታናናሾቻችን ትምህርት እንደሚወስዱም ተስፋ አደርጋለሁ።

*** እግዚዓብሄር ከኔ ጋር ነውና ሁሉም ለበጎ እንደሆነ አስቤ እተወዋለሁ።

የእርሱም ፍቃድ ከሆነ ወደ አርባ በሚጠጉ ባለአክስዮኖች ስለሚቋቋመው የሚዲያ ሴንተርና የቴሌቭዥን ስርጭት ግዜው ሲደርስ መግለጫ እንሰጣለን።

ኢትዮጵያን ለማስደሰት ያብቃን!!!

አብርሃም ወልዴ።
***
#Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
አዝናለሁ! #ETHIOPIA | የራስን ጎጆ ለማሞቅ የጎረቤትን ማቃጠል ወንጀል ነው። አንድ ሰው ወይንም አንድ ድርጅት ስራ ሲጀምር የሚነድፋቸው እቅዶችና ተግባሮች ይኖሩታል። ለሁሉም እንዳግባቡ የግዜ ሰሌዳም ያበጃል። ሂደቱን የሚመለከታቸው አካላት ብቻ እንዲያውቁት የሚመረጥ ግዜ አለ። ቅደም ተከተሉን ጠብቆ ወደ ህብረተሰቡ የሚደርስበትም የራሱ ግዜ አለው። መረጃም ሲሰ'ጥ የመረጃው ልክነትና ልኬት የሚያስጠይቅ ከመሆኑ አንፃር ታስቦ ተመጥኖ መሆን አለበት። ሁሉም አልቆ ግዜው ሲፈቅድ ብቻ ነው ወደ መግለጫና ወደ ዜና የሚቀርበው። የዛም ውሳኔ ባለቤት ለፍተው እዛጋ ያደረሱት የኩባንያው ባለቤቶች ብቻ ናቸው። እንደዚህ የሚባል ወሬ አለ እውነት ከሆነ የሚመለከታቸውን ግለሰቦች አነጋግረን አጣርተን እንመጣለን ማለት አንድ ነው። ባለቤቱ በጉዳዩ ላይ መረጃ መስጠት ካልፈለገና ነገር ግን ጥያቄው ከህዝብ የመጣ ከሆነ መረጃ ሊሰጡን አልቻሉም ተብሎ ማቅረብ የሚቻልበትም ሌላ አግባብ አለ። ትንሽ ፍንጭ ይዞ ያለግዜው የግምት ዝርዝር ይዞ መቅረብ ያልበሰለ እሸት "ቀጥፎ" ያለግዜው መቅጨት ነውና ሊታሰብበት ይገባል። ለምሳሌ ከአንድ ሳምንት በፊት ሰይፉ ፋንታሁን ስልክ ደውሎ ቴሌቪዥን ጣቢያ ልትከፍት ነው የሚል ወሬ ሰማሁ እውነት ነወይ ሲል ጠይቆኛል። ባለቤትነቱ የእኔ ብቻ ያልሆነ በርካታ ህብረተሰቡ የሚወዳቸውና ለሃገራቸው ትልልቅ አስተዋፅዖ ያደረጉ ኢትዮጵያዊያን ባለአክስዮኖችን ጨምሮ በመቋቋም ላይ ያለ የሚዲያ ኩባንያ መሆኑን፤ ብዙ አዳዲስ ነገሮች እንደሚኖረንና በጣም የታሰበበት ከመሆኑ አንፃር ግዜው ሳይደርስ እንዲወራ እንደማንፈልግ ነገር ግን ግዜው ሲደርስ እኔው እንደምደውልለት አደራ ብዬው ስልኩ ተዘጋ። በሚቀጥለውም ቀን ባልደረባው ታደለ አሰፋ የታደለ ሮባ ሰርግ የእራት ግብዣ ላይ ስራዬ ብሎ መጥቶ ሲጠይቀኝ ይሄን ነገር ማስቆም አለብኝ ብዬ ለሰይፉ እንደነገርኩትና ይበልጥ ለማሳሰብ ብዬ ብዙ ነገር እንደሚያበላሽብን አደራ ጨምሬ ነገርኩት። አደራ ምንድነው? መረጃውንስ በትክክል ሳይሆን አበላሽቶ ማውራት ምንድነው? በቅርብ ቀን ማለትስ ከየት ያገኛችሁት መረጃ ነው? ስለ ቴሌቪዥን ቻናሎች መብዛት ትችትን ከዚህ ጋር አያይዞስ ማውራት ምንድነው? ከዚህኛው ርዕስ ተነስቶስ ተመሳሳይ ጣቢያ ስፖንሰር የተደረጉበት በሚመስል ሁኔታ በቅርብ እንደሚከፈትና የዚያኛውን ታላቅነትና አስተማማኝነት ስሜታዊ የሆነ ትንታኔ መስጠትስ ምንድነው? ከዚህ በፊት መግለጫ ልሰጥበት በምፈልገው ትልቅ ጉዳይ ሳነጋግራችሁ ሌላ አካል ፈርታችሁ ከሙያው ስነምግባር ውጪ በመሆን አናቀርብም ብላችሁ አሁን ደግሞ አታቅርቡ ያልኳችሁንስ ማቅረብ ምንድነው? ባለቤትነቱን የኔ ብቻ ማድረጋችሁና በማታውቁት ታሪክ ላይ መሪ ተዋናይ መሆናችሁስ ምንድነው? ብዙ ነገር ያበላሽብናል ብያችሁ አልነበር?.... ለናንተ ጥሩ ዜና አለኝ... ብዙ ነገር አበላሽቷልና እንኳን ደስ አላችሁ!! የራስን ጎጆ ለማሞቅ የጎረቤትን ማቃጠል ወንጀል ነው። የተሰማኝን ሳልደብቅ፣ ሳልቆጥብ መናገሬ የተለመደ ነው ታውቃላችሁ። ከኛ መተቻቸት ታናናሾቻችን ትምህርት እንደሚወስዱም ተስፋ አደርጋለሁ። *** እግዚዓብሄር ከኔ ጋር ነውና ሁሉም ለበጎ እንደሆነ አስቤ እተወዋለሁ። የእርሱም ፍቃድ ከሆነ ወደ አርባ በሚጠጉ ባለአክስዮኖች ስለሚቋቋመው የሚዲያ ሴንተርና የቴሌቭዥን ስርጭት ግዜው ሲደርስ መግለጫ እንሰጣለን። ኢትዮጵያን ለማስደሰት ያብቃን!!! አብርሃም ወልዴ። *** #Getu Temesgen - (ጌጡ ተመስገን)
0 Comments 0 Shares