በቂሊንጦ ብጥብጥ ተነሳ
ታምሩ ጽጌ
Fri, 07/13/2018 - 11:30
በቂሊንጦ ብጥብጥ ተነሳ ታምሩ ጽጌ Fri, 07/13/2018 - 11:30
WWW.ETHIOPIANREPORTER.COM
በቂሊንጦ ብጥብጥ ተነሳ | ሪፖርተር Ethiopian Reporter Amharic
በፌዴራል ማረሚያ ቤቶች አስተዳደር ቂሊንጦ እስረኛ ማቆያ ውስጥ ዓርብ ሐምሌ 6 ቀን 2010 ዓ.ም. ብጥብጥ መነሳቱ ታወቀ፡፡ የታሳሪ ቤተሰቦች ምግብ ለማድረስ ከጠዋቱ ሦስት ሰዓት ጀምሮ በሥፍራው ቢገኙም እንዳይገቡ ተከልክለዋል፡፡ የማረሚያ ቤቱ ጠባቂዎችና አድማ በታኞች በግቢው ውስጥ እየተሯሯጡ ሲሆን፣ ከውስጥ የጩኸት ድምፅ እየተሰማ መሆኑን የታሳሪ ቤተሰቦች ተናግረዋል፡፡ ጠያቂ ቤተሰቦችም የተፈጠረውን ባለማወቃቸው፣ በጭንቀት ውስጥ መሆናቸውን ገልጸዋል፡፡ የተፈጠረውን ችግር በተመለከተ የማረሚያ ቤቱን ኃላፊዎች ምላሽ ማግኘት አልተቻለም፡፡
0 Comments 0 Shares