ባይደን በሔሊን አውሎንፋስ የደረሰውን ጉዳት ለመመልከት ወደ ፍሎሪዳ እና ጆርጂያ ያቀናሉ
የዩናይትድ ስቴትስ ፕሬዝዳንት ጆ ባይደን በሔሊን አውሎንፋስ ጉዳት የደረሰባቸውን አካባቢዎች ለመጎብኘት ዛሬ ሐሙስ ወደ ፍሎሪዳ እና ጆርጂያ ግዛቶች እንደሚያመሩ ተገለጠ። በአደጋው ምላሽ ጥረቶች ላይ ከተሳተፉ የመጀመሪያ እርዳታ ሰጪዎች እና የአካባቢው ባለሥልጣናት ጋርም ይገናኛሉ።
ረቡዕ እለት ባይደን የሰሜን እና ደቡብ ካሮላይና ግዛቶችን የጎበኙ ሲሆን፣ ሔሊን በሰሜን ካሮላይና ያደረሰውን ጉዳት በሄሊኮፕተር ተዘዋውረው ከተመለከቱ በኃላ "አውሎንፋሱ ያደረሰውን ጉዳት...