AMHARIC.VOANEWS.COM
በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለው ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እስራቶች ተቀጣ
በደቡብ አፍሪካ በ90 አስገድዶ መድፈሮች ጥፋተኛ የተባለ ግለሰብ በ42 የዕድሜ ልክ እሥራቶች ተቀጥቷል። የ40 ዓመት ዕድሜ ያለው ንኮሲናቲ ፋካቲ የዘጠኝ ዓመት ዕድሜ ያላቸው ልጆች ላይ ጭምር በፈፀመው አስገድዶ መድፈር፣ ሌሎች ልጆች ድርጊቱን እንዲመለከቱ ያስገድድ ነበር ተብሏል። ግለሰቡ ድርጊቱን የፈፀመው ከእ.አ.አ 2012 እስከ 2021 ባለ ጊዜ ውስጥ ከጆሃንስበርግ በስተ ምሥራቅ በምትገኝ መንደር ወዳለ ትምህርት ቤት የሚሄዱ ልጆችን ዒላማ በማድረግ ነበር።...
0 Comments 0 Shares