እስራኤል የቤሩትን አካባቢ ስትደበድብ አመሸች
እስራኤል ምሽቱን በቤሩትና አካባቢዋ ተከታታይና ከፍተኛ የተባለ የአየር ጥቃት ፈፅማለች፡፡ የአየር ድብደባው በሌባኖስ እና በሶሪያ መካከል የሚገኝን የድንበር መተላለፊያ ላይ በመፈጸሙም፣ በአስር ሺሕ የሚቆጠሩ ሰዎች ከጥቃቱ መሸሽ እንዳይችሉ አድርጓል።
ከቤሩት ዳርቻ ባለ የመኖሪያ አካባቢ የተከሰተው ከፍተኛ ፍንዳታ፣ ጭስና ነበልባል በምሽቱ ሰማይ ላይ ሲያሳይ፣ ንዝረቱ በኪሎሜትሮች ርቀት ላይ በመዲናዋ በሚገኙ ሕንፃዎች ላይ ተሰምቷል።
ከቤሩት 48 ኪሎሜትር ርቀት...