የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤት ከአምስት አባላቱ ክስ ቀረበበት
የኢትዮጵያ የፖለቲካ ፓርቲዎች የጋራ ምክር ቤቱ የሥራ አስፈጻሚ አባላት ያበቃውን ሥልጣናቸውን በሕገወጥ መንገድ ለማራዘም ጥረት እያደረጉ ነው ሲሉ አምስት ፓርቲዎች አቤቱታ አቀረቡ
ምርጫ ቦርድ፣ አስቸኳይ ጠቅላላ ጉባዔ ጠርቶ የጋራ ምክር ቤቱን የሚመሩ አመራሮችን እንዲያስመርጥም ፓርቲዎቹ ጠይቀዋል፡፡
ከበርካታ አባል ፓርቲዎች ውስጥ አቤቱታውን ያቀረቡት አምስት ብቻ መሆናቸውን የጠቀሱት የምክር ቤቱ ሰብሳቢ አቶ ደስታ ዲንቃ በበኩላቸው፣ “የሥራ አስፈጻሚ አባላት...