በአላማጣ ከተማ ከህወሓት ታጣቂዎች ጋር ተፈጠረ ባሉት ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ነዋሪዎች ተናገሩ
በአላማጣ ከተማ፣ “የትግራይ ክልልን ስርዓተ ትምህርት መሠረት ያደረገ የትምህርት ምዝገባ ተጀምሯል” በሚል ተቃውሞ ለመግለጽ በወጡ ወጣቶችና "የህወሓት ታጣቂዎች" ሲሉ በገለጿቸው አካላት መካከል ተፈጠረ ባሉት ግጭት የሁለት ሰዎች ህይወት ማለፉን ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናግረዋል።
በአማራ ክልል የበጀትና አስተዳደራዊ ድጋፍ የተቋቋመው የከተማው ጊዜያዊ አስተዳደር ከንቲባ መሆናቸውን የገለፁት ኃይሉ አበራ ለጥቃቱ “በተፈናቃይ ስም ወደ አካባቢው ገብተዋል” ያሏቸውንና...