ኢትዮጵያውያን ልዩነቶቻቸውን ከግጭት ይልቅ በውይይት መፍታት ላይ እንዲያተኩሩ አሜሪካ ጥሪ አቀረበች
ዩናይትድ ስቴትስ በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች በሰላም እንዲፈቱ ጥረቷን እንደምትቀጥል የአገሪቱ አምባሳደር ጥሪ አቀረቡ።
አምባሳደሩ ኧርቪን ማሲንጋ፣የዩናይትድስቴትስ ዓለምአቀፍ የልማት ተራድኦ ድርጅት በምህጻሩ የዩኤስኤአይዲ የአምስት ዓመት “የኢትዮጵያ ድጋፍ ፕሮግራም” ማጠቃለያ ዝግጅት ላይ ባደረጉት ንግግር፣ በኢትዮጵያ ያሉ ግጭቶች የአገሪቱ የኢኮኖሚ እድገት እንዲያሽቆለቁል ማድረግን ጨምሮ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች እና የማህበራዊ አገልግሎት ተቋማት ውድመት እንዲቀጥል...