እስራኤል ሌላ ተጨማሪ የሄዝቦላ ከፍተኛ አመራር መግደሏን አስታወቀች
እስራኤል የሄዝቦላው መሪ ሀሰን ናስረላህ ከተገደሉ ጥቂት ቀናት በኋላ ትላንት ቅዳሜ የቡድኑን ሌላ ከፍተኛ አመራር አባል መግደሏን ዛሬ አስታወቀች፡፡
በኢራን የሚደገፈው ታጣቂ ሄዝቦላህ ቡድን ከፍተኛ አመራር መግደሉን ያስታወቀው የሄዝቦላ መቀመጫ በሆነችው ሊባኖስ ላይ ጥቃቱን የቀጠለው የእስራኤል ጦር ነው፡፡
በጥቃቱ የተገደሉት የሄዝቦላህ ማዕከላዊ ምክር ቤት ዋና ሃላፊ የሆኑትን ናቢል ካዓውክ መሆናቸውን የእስራኤል ጦር በዛሬው መግለጫው አመልክቷል፡፡
እስራኤል...