የአማራ ክልል ግጭት በሰላም እንዲፈታ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ ጫና እንዲያደርግ ካውንስሉ ጠየቀ
ዩናይትድ ስቴትስን ጨምሮ ዓለም አቀፉ ማኅበረሰብ፣ የአማራ ክልል ግጭት ሰላማዊ መፍትሔ እንዲያገኝ በተፋላሚ ኃይሎች ላይ ጫና እንዲፈጥሩ የክልሉ የሰላም ካውንስል ጠይቋል፡፡
በመንግሥት ኃይሎች እና በፋኖ መካከል በሚደረገው የግጭት ዐውድ ውስጥ የሚፈፀመው የሰብዓዊ መብቶች ጥሰት አሳሳቢ ሆኖ መቀጠሉን የገለፀው ኢሰመኮ ግጭቱ በውይይት እንዲፈታ ከትላንት በስቲያ መጠየቁ ይታወቃል፡፡
የአማራ ክልል የሰላም ካውንስልሰብሳቢ ያየህይራድ በለጠ ለአሜሪካ ድምፅ በሰጡት...