የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ከፍተኛ አመራር አባል ጃል ሰኝ ነጋሳ ከድርጅቱ መነጠላቸውን አስታወቁ
በጃል መሮ ወይም ኩምሳ ድሪባ ከሚመራው የኦሮሞ ነጻነት ሠራዊት ራሳችንን አግልለናል ሲሉ የድርጅቱ የሥራ አስፈፃሚ ኮሚቴ አባልና የማዕከላዊ ዞን የቀድሞ አዛዥ ጃል ሰኝ ነጋሳ አስታውቀዋል።
ጃል ሰኝ ነጋሳ መሆናቸውን ያስተዋወቁት የድርጅቱ አመራር፣ ከተመረጡ መገናኛ ብዙሀን ዘጋቢዎች በስልክ ለቀረቡላቸው ጥያቄዎች የት እንደሆኑ ባልተገለፀ ቦታ ሆነው በሰጡት ምላሽ፣ ረቡዕ መስከረም 15 ቀን 2017 ዓ/ም የወጣውና የማዕከላዊ ዞን ዕዝ፣ በጃል መሮ ወይም ኩምሳ ድሪባ...