ጉባኤ ያካሄዱ የህወሓት አመራሮች የጊዚያዊ ካቢኔ መግለጫ ተቃወሙ
ጉባኤ ያካሄዱ የህወሓት አመራሮች ትላንት ማክሰኞ አመሻሽ ላይ ባወጡት መግለጫ: የትግራይ ክልል የፀጥታ ሓይሎች በአስተዳደሩ ስር መሆን አይገባውም ሲሉ የክልሉን አስተዳደር ካቢኔ ውሳኔ እንደሚቃወሙ ገለፁ፡፡
"በአሁኑ ግዜ በህወሓት ውስጥ ክፍፍል እንዳለ ለማሳየት፣ በክልሉ አስተዳደር የቀረበው አገላለጽ ተቀባይነት የለውም" ያለው መግለጫቸው "ልዩነቱ ያለው ህወሓትን በማዳን የትግራይን ህዝብ ጥቅም ለማረጋገጥ በሚጥር ፓርቲ እና በሂደት ከትግል ወጥቶ ፓርቲውን እና...