በጦርነት በምትታመሰው ሱዳን የኮሌራ በሽታ እየተስፋፋ ነው
በጦርነት በምትታመሰው ሱዳን የኮሌራ በሽታ እየተስፋፋ መሆኑን እና ባለፉት ሁለት ወራት ውስጥ ብቻ ቢያንስ 388 ሰዎች ህይወታቸው ሲያልፍ ወደ 13 ሺህ የሚጠጉ ለህመም መዳረጋቸውን የጤና ባለሙያዎች አስታውቀዋል።
በሽታው በተለይ በጦርነቱ የተፈናቀሉ በሚሊየኖች የሚቆጠሩ ሰዎች በሚገኙበት ምስራቃዊው የሱዳን ክፍል በቅርቡ በጣለው ከባድ ዝናብ እና ጎርፍ መባባሱም ተጠቁሟል። የሱዳን ጤና ሚኒስቴር እሁድ እለት ባወጣው ሪፖርት፣ ባለፈው ሳምንት መጨረሻ ብቻ በኮሌራ ጉዳት...