"ዩናይትድ ስቴትስ ለአፍሪካ ሀገሮች አንድ ሚሊዮን የኤም ፖክስ ክትባት ትለግሳለች" ፕሬዚደንት ባይደን
ዩናይትድ ስቴትስ የአፍሪካ ሀገሮች የያዙት የጸረ ኤም ፖክስ ወረርሽኝ ትግል ለመደገፍ አንድ ሚሊዮን ክትባቶችን እና ቢያንስ የአምስት መቶ ሚሊዮን ዶላር እርዳታ መስጠቷን ፕሬዚደንት ጆ ባይደን ዛሬ አስታወቁ።
ዛሬ ማክሰኞ ለተባበሩት መንግሥታት ድርጅት ጠቅላላ ጉባኤ ባሰሙት ንግግር እርዳታውን ይፋ ያደረጉት ፕሬዚደንት ባይደን ሊሎች ሀገሮችም ተመሳሳይ እርዳታ እንዲያደርጉ ተማጽነዋል። "ኤምፖክስን ለመጋፈጥ ፈጥነን መንቀሳቀስ አለብን " ብለዋል ባይደን።
የዓለም...