በሩስያ ሚሳኤል ጥቃት ሶስት ሰዎች መገደላቸውን ዩክሬን አስታወቀች
በማዕከላዊ ዩክሬን ክሪቪ ሪህ ሌሊቱን በድረሰ የሩስያ የሚሳኤል ጥቃት አንድ የ12 አመት ወንድ ልጅ እና ሁለት አረጋውያን ሴቶች መሞታቸውን የአካባቢው አስተዳዳሪ ሰርሂ ሊሳክ ዛሬ ቅዳሜ አስታውቀዋል።
"እኩለ ሌሊት ላይ ከተማዋ ባሸለበችበት እንደገና አስፈሪ የጠላት ጥቃት በኪሪቪ ሪህ ላይ ደርሷል " ሲሉ አስተዳዳሪው ሊሳክ በቴሌግራም ላይ በጽፉት መልዕክት ተናግረዋል፡፡
ተጨማሪ ሶስት ሰዎች ቆስለው ወደ ሆስፒታል መወሰዳቸውንም ተናግረዋል። በጥቃቱ የተገደሉት...