ግጭት ባለባቸው አንዳንዶቹ የኦሮሚያ ዞኖች የስልክ አገልግሎት መቋረጡን ነዋሪዎች ተናገሩ
በኦሮሚያ ክልል ሰሜን ሸዋ ዞን እንደዚሁም ምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች፣ የስልክ አገልግሎት ረዘም ላለ ጊዜ መቋረጡን የገለጹ የአካባቢው ነዋሪዎች፣ በኢኮኖሚያዊና በማህበራዊ እንቅስቃሴዎች ከፍተኛ ተጽእኖ እያደረሰ መሆኑን ተናገሩ።
የአገልግሎቱ መቋረጥ ከአካባቢው የጸጥታ ችግር ጋራ ተዳምሮ፣ አሳሳቢ እንደሆነባቸውም አመልክተዋል።
በምዕራብ ወለጋ እና ቄለም ወለጋ ዞኖች በሚገኙ በርካታ ወረዳዎች ፣ በተለይ የኢንተርኔት አግልግሎት ከተቋረጠ ከአራት ዓመታት...