ባይደን የኳድ መሪዎችን ስብሰባ በመኖሪያ ቤታችው ያስተናግዳሉ
ፕሬዝደንት ባይደን በመጪው ቅዳሜ የአውስትራሊያ፣ ህንድና ጃፓን መሪዎችን ተቀብለው “ኳድ” በሚል የሚታወቀውን የአራቱን ሃገራት ቡድን ስብሰባ ያስተናግዳሉ። ቡድኑ በተለይም በኢንዶ ፓሲፊክ ቀጠና ባለ ስልታዊ የፀጥታ ትብብር ላይ ያተኩራል። ሕዝብ በብዛት የሚገኝበት ቀጠናው ለቻይናም ከኢኮኖሚ እና ከስልት አንጻር ወሳኝ ነው።
“ኳድ” በሚል መጠሪያ የሚታወቀውን የህንድ፣ ጃፓን አውስትራሊያ እና አሜሪካ የቡድን ግንኙነት ወደ በለጠ ደረጃ ማሳደግ የፕሬዝደንት ባይደን ዋና...