በአማራ ክልል ምስራቅ ጎጃም ሁለት መምህራን መገደላቸውን የአካባቢው አስተዳደር አስታወቀ
“በአማራ ክልል፣ ምስራቅ ጎጃም ዞን ስናን ወረዳ፣ ሁለት የሁለተኛ ደረጃ ት/ቤት መምህራን ትናንት መስከረም 8/2017 ዓ.ም. በፋኖ ታጣቂዎች ተገድለዋል” ሲል የአካባቢው አስተዳደር አስታወቀ።
የአሜሪካ ድምፅ ያነጋገራቸው የስናን ወረዳ አስተዳዳሪ አየነው ደለለ፣ ሁለቱ መምህራን የተገደሉት በፋኖ ታጣቂዎች ከመኖሪያ ቤታቸው ከተወሰዱ በኋላ መሆኑን ገልጸዋል።
“ታጣቂዎቹ መምህራኑን የገደሉት፣ ትምህርት ለማስጀመር እንቅስቃሴ አድርጋችኋል በማለት ነው” ሲሉም...