በቱኒዚያ የፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዘመቻ ቅስቀሳ ተጀመረ
የቱኒዚያ የፕሬዝዳንታዊ የምርጫ ወቅት ቅስቀሳ ትላንት ቅዳሜ በይፋ ተጀምሯል፡፡ ይህም የሃገሪቱ ሁኔታ እያሸቆለቆለ ነው ያሉ ቱኒዚያውያን ቁጣቸውን በዋና ከተማው ጎዳናዎች ላይ በመውጣት ከገለጹ ማግስት ነው፡፡
በዚህ አመት መጀመሪያ ላይ ባለስልጣናት ለወራት የዘለቀ የእስር ማዕበል ከጀመሩበት ጊዜ አንስቶ ትልቁ በሚመስለው ተቃውሞ፣ አርብ ዕለት በመቶዎች የሚቆጠሩ ቱኒዚያውያን ሰላማዊ ሰልፍ በማካሄድ የ “ ፖሊስ መንግስት” ሲሉ የጠሩት ይህ ድርጊት እንዲያበቃ...