ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒዤር የጋራ ፓስፖርት ሊጠቀሙ ነው
ማሊ፣ ቡርኪና ፋሶ እና ኒዤር በቅርቡ አዲስ የባዮሜትሪክስ ፓስፖርት በሥራ ላይ እንደሚያውሉ የማሊው ወታደራዊ መሪ ኮሎኔል አሲሚ ጎይታ ትላንት እሁድ አስታውቀዋል።
ሦስቱ የሳህል ቀጠና ሃገራት ከእ.አ.አ 2020 ጀምሮ በተከታታይ የተፈጸሙ መፈንቅለ መንግስቶችን ተከትሎ በወታደራዊ አገዛዝ ሥር ይገኛሉ።
ሦስቱ ሃገራት ባለፈው ዓመት መስከረም ወር ላይ ከቀጠናው የኢኮኖሚ ማኅበረሰብ (ኤኮዋስ) ተገንጥለው በመውጣት ‘የሳህል ሃገራት ትብብር’ መሥርተዋል። ሃገራቱ...