በኮሪደሩ ልማት “በአጭር ጊዜ ውስጥ ትነሳላችኹ በመባላችን ስጋት ገብቶናል” የየካ ክፍለ ከተማ ነዋሪዎች
“በቂ ውይይት ሳይደረግ እና መተማመን ላይ ሳይደረስ የሚነሳ ነዋሪ የለም” ክፍለ ከተማው
በአዲስ አበባ፣ የየካ ክፍለከተማ አንዳንድ ነዋሪዎች፣ “በኮሪደር ልማት ምክንያት “በአጭር ጊዜ ውስጥ ትነሳላችኹ” መባላቸውን ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቁ፡፡ ነዋሪዎቹ በሰጡት አስተያየት “ከህዝቡ ጋራ ውይይት ሳይደረግ፣ የምንዘጋጅበት በቂ ጊዜም ሳይሰጠን፣ ትነሳላችኹ በመባላችን ስጋት ገብቶናል” ሲሉ ቅሬታቸውን ገልፀዋል፡፡
የየካ ክፍለ ከተማ በበኩሉ፣ ነዋሪዎችን ለማስነሳት...