በመንበረ ሰላማ ተፈጸመ ያሉትን ሹም ሽረት ያልተቀበሉ የአላማጣ ነዋሪዎች ተቃውሞ አሰሙ
በትግራይ የተቋቋመውና “መንበረ ሰላማ ከፍተኛ ቤተ ክህነት” ተብሎ የሚጠራው ተቋም፣ ከኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ስርአት ውጭ በሆነ መልኩ በራያና አካባቢው የራሱን አስተምህሮና አስተዳደራዊ ስርአት በመዘርጋት ላይ ነው ያሉ የአላማጣ ከተማ ኗሪዎች ተቃወሟቸውን ትናንት በሰላማዊ ሰልፍ ገለጹ፡፡
በአካባቢው ያሉት አብያተክርስቲያናት፣ በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ ስር እንደቆዩ የሚናገሩት የራያና አካባቢው አገረስብከት ስራ...