አውሎ ነፋስ ‘ፍራንሲን’ የኃይል መቋረጥና ጎርፍ አስከተለች
‘ፍራንሲን’ በሚል የተሰየመችው ነፋስ የቀላቀለች አውሎ ነፋስ በአሜሪካ ሉዊዚያና ግዛት በሰፊው የኤሌክትሪክ የኃይል አቅርቦት እንዲቋረጥ ስታደርግ፣ በባሕር ዳርቻው አካባቢ የሚገኙ አካባቢዎች ላይ አደገኛ ዝናብና ነፋስ አስከትላለች፡፡
ሆኖም ግን ወደ ሚሲሲፒ ግዛት እየተቃረበች ስትመጣ ኃይሏ እየቀነሰ እንደመጣ የአሜሪካው ብሔራዊ የአውሎ ነፋስ መከታተያ ማዕከል አስታውቋል።
ፍራንሲን ትላንት ምሽት ሉዊዚያና ላይ ስታርፍ ፍጥነቷ 100 ማይል በሰዓት ነበር። በኒው...