በኢትዮጵያ እና በሶማሊያ መካከል ባለው ውጥረት የዩናይትድ ስቴትስ አቋም
ኢትዮጵያ ከራስ ገዟ የሶማሌላንድ አስተዳደር ጋር የተፈራረመችውን አወዛጋቢ የመግባቢያ ሥምምነት ተከትሎ፤ በሶማሊያ እና በኢትዮጵያ መካከል ለተፈጠረው ውጥረት ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ይገኛል የሚል ተስፋ ማሳደራቸውን አንድ የዩናይትድ ስቴትስ ዲፕሎማት ገለጡ።
በሞቃዲሾ የዩናይትድ ስቴትስ አምባሳደር ሪቻርድ ራይሊ ከአሜሪካ ድምጽ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ ሃገራቸው “ለዚህ ወቅታዊ ሁኔታ ዲፕሎማሲያዊ መፍትሄ ለማፈላለግ ከሌሎች ጋር በትብብር እየሰራች ነው” ብለዋል።...