የማሊ ወታደራዊ ጁንታ የፈረንሳይኛ ቋንቋ ቴሌቪዥንን ለ3 ወር አገደ
የማሊ ወታደራዊ ጁንታ ቲቪ ፋይቭ ሞንዴ (TV5 Monde) ተብሎ የሚጠራውን በፈረንሳይ ቋንቋ የሚያሰራጭ የቴሌቭዥን ጣቢያ ለሦስት ወራት አገደ፡፡
ገዥው የማሊ ወታደራዊ መንግሥት የቴሌቪዥን ጣቢያውን ያገደው በዜና ዘገባው ላይ “ሚዛናዊነት” የጎደለው በመሆኑ ነው ሲል መንግሥታዊው የመገናኛ ብዙኃን ተቆጣጣሪው መሥሪያ መግለጹን ኤኤፍፒ ዛሬ ረቡዕ የደረሰውን መግለጫ ጠቅሶ ዘግቧል፡፡
ከፍተኛ የኮሙዩኒኬሽን ጉዳዮች ባለሥልጣን የቴሌቭዥን ጣቢያው በሰሜናዊቷ ቲንዛኦዋቴን...