በሱዳን ጦርነት ቢያንስ 20 ሺህ ሰዎች መሞታቸውን ተመድ አስታወቀ
በሱዳን ከ16 ወራት በላይ በዘለቀው ጦርነት ከ20 ሺህ በላይ ሰዎች መሞታቸውን የተባበሩት መንግስታት ድርጅት ከፍተኛ ባለስልጣን ትላንት እሁድ አስታወቁ።
የዓለም ጤና ድርጅት ዋና ዳይሬክተር ቴድሮስ አድሃኖም ገብረ ኢየሱስ ዓለም አቀፍ ዕውቅና ያለው በጦር ሠራዊቱ የሚደገፈው የሱዳን መንግሥት መቀመጫ በሆነችው ፖርት ሱዳን ከተማ በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ የሟቾች ቁጥር ከዚህ በላይ ሊሆን እንደሚችልም አመልክተዋል።
ቴድሮስ በሱዳን ያካሄዱትን የሁለት ቀናት ጉብኝት...