በኒውዮርክ የአይሁድ ማዕከልን ለማጥቃት አሲሯል የተባለው ፓክስታናዊ ተከሰሰ
በኒውዮርክ ከተማ እስላማዊ መንግስትን በመደገፍ የጅምላ ጥቃት ለማካሄድ አቅዷል በሚል የ20 ዓመቱ ፓኪስታናዊ መሀመድ ሻህዜብ ካን ተከሰሰ፡፡
ጥፋተኝነቱ ከተረጋገጠ "እስከ 20 አመት የሚደርስ እስራት ይጠብቀዋል" ሲል የዩናትይድስ ፍትህ ሚኒስቴር ትላንት ዐርብ ባወጣው መግለጫ አመልክቷል፡፡
ካን የተከሰሰው በእስራኤል የሐማስ ጥቃት የተካሄደበት አንደኛ ዓመት በሚታሰብበት እኤአ ጥቅምት 7 ቀን፣ በኒውዮርክ ብሩክሊን በሚገኘው የአይሁድ ማእከል ላይ ጥቃት ለመሰንዘር...