“ማንም ኢትዮጵያን መድፈር ሲፈልግ አንድ ጊዜ ሳይሆን አስር ጊዜ ማሰብ ይኖርበታል” ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ
"የሉዓላዊነት ቀን" በሚል በመላው አገሪቱ ከተከናወኑት መርሃ-ግብሮች በአንዱ ላይ የተገኙት ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ "በኛ በኩል ምንም አይነት የጦርነት፣ የግጭት ፍላጎት የለንም" ሲሉ አክለዋል።
ኢትዮጵያ ታኅሳስ 22 ቀን 2016 ዓ/ም ከሶማሌላንድ ጋር የተፈራረመችውን የመግባቢያ ስምምነት ተከትሎ፣ ከሶማሊያ ጋር ያለው ዲፕሎማሲያዊ ውዝግብ በቀጠለበት ወቅት የተደረገው የጠቅላይ ሚንስትሩ ንግግር የትኛውንም አገር በስም አልጠቀሰም።
የሶማሊያ መሪዎች በተለያያ ጊዜ...