በኬንያ በአንድ ት/ቤት በደረሰ የእሳት አደጋ 17 ተማሪዎች መሞታቸው ተገለጠ
በኬንያ በአንድ የአንደኛ ደረጃ ት/ቤት በትላንትናው ምሽት በደረሰ የእሳት አደጋ 17 ተማሪዎች ሕይወታቸውን ሲያጡ፣ ሌሎች 13 የሚሆኑ ክፉኛ መጎዳታቸው ታውቋል።
የሟቾቹ ቁጥር ከተጠቀሰውም ሊያሻቅብ እንደሚችል ፖሊስ ስጋቱን ገልጿል። የእሳቱ መነሻ ምክንያትንም እየመረመረ መሆኑን አስታውቋል።
ኒየሪ በተሰኘው አውራጃ በሚገኘው በዚህ ት/ቤት ውስጥ አደጋው በደረሰበት ምሽት 150 የሚሆኑ ዕድሜያቸው ከ14 ዓመት በታች የሆኑ ተማሪዎች እንቅልፍ ላይ እንደነበሩም...