በደቡብ ሱዳን ጎርፍ የ700 ሺሕ ሰዎችን ሕይወት አመሳቀለ
በደቡብ ሱዳን በመድረስ ላይ ያለው የጎርፍ አደጋ ከ700 ሺሕ በላይ የሚሆኑ ሰዎችን ለችግር እንደዳረገ በተባበሩት መንግስታት ድርጅት የሰብዓዊ ጉዳዮች ጽ/ቤት አስታውቋል።
ጎርፍ የመኖሪያ ቤቶችን፣ ሰብል እና መሠረተ ልማቶችን ሲያወድም፣ የትምህርትና የጤና አገልግሎቶች እንዲቋረጡ ማድረጉን፣ በሽታም እንዳይዛመት ሥጋት መፍጠሩን በተመድ የሰብዓዊ ጉዳዮች ማስተባበሪያ ቢሮ (ኦቻ) ትላንት ሐሙስ ባወጣው ሪፖርት አስታውቋል።
ጎርፍ፤ በሃገሪቱ ከሚገኙ 78 አውራጃዎች...