በመተማ በኩል ያለው የኢትዮጵያ እና የሱዳን ድንበር ተዘጋ
በምዕራብ ጎንደር አካባቢዎች በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ፣ በመተማ በኩል ያለው የኢትዮጵያና የሱዳን ድንበር ዘመጋቱን የመተማ ዮሃንስ ከተማ ነዋሪዎች ለአሜሪካ ድምፅ ተናገሩ፡፡ ጉዳዩን አስመልክቶ ለአሜሪካ ድምፅ በኢሜይል ማብራሪያ የሰጠው የመንግስታቱ ድርጅት የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር (ዩኤንኤችሲአር) በመንግስት የፀጥታ ኃይሎች እና ባልታወቁ ታጣቂዎች መካከል ባለው ግጭት የተነሳ ኢትዮጵያን ከሱዳን የሚያገናኘው የጋላባት-መተማ ድንበር መዘጋቱን አስታውቋል፡፡...