የዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ኩሌባ የሥራ መልቀቂያ አቀረቡ
የዩክሬን ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዲሚትሮ ኩሌባ ዛሬ ረቡዕ የሥራ መልቀቂያ አቀረቡ፡፡
በዓለም አቀፍ ደረጃ ዩክሬንን በመወከል ታዋቂ ከነበሩት መካከል አንዱ የሆኑት የ43 ዓመቱ ኩሌባ ከሥልጣን ለመልቀቅ የፈለጉበትን ምክንያት አላቀረቡም፡፡
የመልቀቂያው ጥያቄቸውን ምክር ቤቱ በሚቀጥለው ስብሰባ እንደሚነጋገርበት የምክር ቤቱ አፈጉባኤ ሩስላን ስቴፋንቸክ በፌስ ቡክ ገጻቸው ተናግረዋል፡፡
ኩሌባ መልቀቂያውን ያቀረቡት ፕሬዝደንት ቮሎድሚር ዜለንስኪ ለጦርነቱ ቀጣይ ወሳኝ...