የቻይና-አፍሪካ ትብብር ጉባኤ ተጀመረ
ኢትዮጵያን ጨምሮ ከ50 የአፍሪካ ሀገራት መሪዎች የታደሙበት የቻይና-አፍሪካ የትብብር ጉባዔ ዛሬ በቤጂንግ ተከፍቷል። ለሦስት ቀናት በሚካሔደው በዚህ ጉባኤ ላይ፣ እስከ አውሮፓውያኑ 2027 በሚኖረው የቻይና እና አፍሪካ ግንኙነት የትብብር ሰነዶች ላይ ውይይት ተደርጎ ስምምነት እንደሚፈረም ይጠበቃል፡፡
በጉባኤው ለመሳተፍ ቤጂንግ ከገቡ የአፍሪካ መሪዎች አንዱ የሆኑት፣ የኢትዮጵያው ጠቅላይ ሚንስትር ዐቢይ አሕመድ፣ ቻይና አበርክታለች ያሉትን ድጋፍ አድንቀዋል፡፡...