የትግራይ ጊዜያዊ አስተዳደር ከክልሉ ከተሞች ነዋሪዎች ጋር የያዘው ውይይት
ከተለያዩ የክልሉ ከተሞች ነዋሪዎች ጋር ህዝባዊ ውይይት ማካሄድ የጀመሩት የትግራይ ክልል ጊዜያዊ አስተዳደር ፕሬዝዳንት ጌታቸው ረዳ፣ ውይይቱ አስተዳደሩ ያሉበትን ክፍተቶች ለማረምና አዎንታዊ ነገሮችን ለማስቀጠል እንደሚያግዝ ጠቅሰዋል። አቶ ጌታቸው፣ ትላንት ማክሰኞ፣በዓዲግራት ከተማ በነበረው ውይይት ላይ ባደረጉት ገለጻ፣ ጊዜያዊ አስተዳደሩን በሚመሩት ሰዎች ላይ "ከፍተኛ የሆነ ስም የማጥፋት ሥራ ተፈጽሟል" ሲሉ ተችተዋል።
በቅርቡ በተካሄደው 14ኛው የህወሓት ጉባኤ...