ዩናይትድ ስቴትስ ከሞስኮ ጋራ ግንኙነት ባላቸው ኩባንያዎችና ሠራተኞቻቸው ላይ ማዕቀብ ጣለች
ሩሲያ፤ በአሜሪካ ማኅበረሰብ ላይና በመጪው ፕሬዝደንታዊ ምርጫ ውጤት ላይ ተጽእኖ ለማሳደር፣ አደገኛ የሃሰት መረጃ የማሰራጨት ዘመቻ በማድረግ ላይ ነች በሚል፣ የአሜሪካ መንግስት ትላንት ረቡዕ ከሞስኮ ጋራ ግንኙነት ባላቸው ኩባንያዎችና ሠራተኞቻቸው ላይ ክስ መስርቶ ማዕቀብ ጥሏል። ሌሎችንም እርምጃዎችን መውሰዱንም አስታውቋል።
በአሜሪካ የፍትህ እና የውጪ ጉዳይ ሚኒስቴር መሥሪያ ቤቶች እንዲሁም ዋናው ግምጃ ቤት በጋራ እንዳስታወቁት፣ ሩሲያ፣ የፕሬዝደንት ቭላድሚር...