ኬንያ በግድያ ወንጀል ተጠርጣሪውን ለአሜሪካ አሳልፋ ሰጠች
በአሜሪካ የሴት ጓደኛውን ገድሎ ወደ ኬንያ ሸሽቷል የተባለ ግለሰብ ለአሜሪካ ተላልፎ መሰጠቱን የኬንያ አቃቢያነ ሕግ ዛሬ አስታውቀዋል።
ባለፈው ኅዳር ወር የሴት ጓደኛውን በባስተን ሎጋን አየር ማረፊያ መኪና ማቆሚያ ሥፍራ በስለት ወግቶ በመግደል ወደ ኬንያ ሸሽቷል የተባለው ተጠርጣሪ ኬቭን ካንጌቲ፣ በጥር ወር በቁጥጥር ሥር ቢውልም፣ ከአንድ ሳምንት በኋላ ከናይሮቢ እስር ቤት በማምለጡ ለሶሶት ወራት ሲፈለግ ቆይቶ እንደገና ተይዞ ነበር። ክስተቱ የኬንያን ፖሊስ...