በእስራኤል ከፍተኛ የሥራ ማቆም አድማ በመደረግ ላይ ነው
የእስራኤል መንግስት ከሐማስ ጋራ የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ እንዲደረስ ግፊት ለማድረግ በሚል ትልቁ የሠራተኛ ማኅበር በጠራው የሥራ ማቆም አድማ ባንኮች፣ የሕዝብ መጓጓዣዎች፣ ሆስፒታሎች፣ የንግድ ሱቆችና ዋናው የአየር ማረፊያ አገልግሎታቸው ተስተጓጉሎ ውሏል።
አድማው የተጠራው በሐማስ እጅ የነበሩ ስድስት ታጋቾች ተገድለው መገኘታቸውን ተከትሎ ነው።
የሠራተኛ ማኅበሩ ሊቀ መንበር አረን ባር-ዴቪድ በጋዛ በሐማስ የታገቱትን ማስለቀቅ “እጅግ አንገብጋቢው ጉዳይ...