AMHARIC.VOANEWS.COM
የስድስት እስራኤላውያን ታጋቾችን መገደል በእስራኤል በሺዎች ለተቃውሞ አደባባይ ወጡ
የስድስት እስራኤላዊያን ታጋቾች አስከሬኖች በደቡባዊ ጋዛ በሚገኝ በምድር ውስጥ ለውስጥ መተላለፊያ ዋሻ መገኘታቸውን ተከትሎ እስራኤላዊያን ድንጋጤ እና ቁጣቸውን መግለጻቸውን ቀጥለዋል። አንዳንዶቹም የሀገሪቱን መንግሥት ከሐማስ ጋር ቀደም ብሎ ከሐማስ ጋር የተኩስ አቁም ስምምነት ላይ ለመድረስ ባለመቻል ወንጅለዋል። ዛሬ ሰኞ በትልቁ የእስራኤል የሠራተኛ ማሕበር የተጠራ አገር አቀፍ የሥራ ማቆም አድማ ተካሂዷል። ሙሉ ዘገባውን ከተያያዘው የድምጽ ፋይል ያድምጡ።
0 Comments 0 Shares