ኮንጎ ውስጥ ከወህኒ ቤት ለማምለጥ በተደረገ ሙከራ ላይ 129 ሰዎች መገደላቸው ተሰማ
ኮንጎ ዲሞክራቲክ ሪፐብሊክ ውስጥ እስረኞች ከወህኒ ቤት ለማምለጥ ሲሞክሩ 129 ሰዎች መገደላቸው ተገለጠ።
የመንግሥቱ ቃል አቀባይ በኤክስ ገጻቸው ላይ እንዳስታወቁት የጸጥታ ኅይሎች ትላንት ሰኞ ማለዳ በዋና ከተማዋ ኪንሻሳ ከሚገኘው ከትልቁ ወህኒ ቤት እስረኞች ሰብረው ሊያመልጡ ሲሉ ከባድ ተኩስ ተነስቷል። የጸጥታ ኃይሎች የወህኒ ቤቱን አካባቢ አጥረውታል።
ከወህኒ ቤቱ የወጡ ምስሎች 24 ሊያመልጡ የሞከሩ እስረኞች እጅግ ከተጨናነቀው የማካላ ማዕከላዊ እስር ቤት...