የዩጋንዳ ተቃዋሚ መሪ ቦቢ ዋይን በጥይት መመታቱን ፓርቲው አስታወቀ
በዩጋንዳ ለበርካታ ዓመታት ስልጣን ላይ ያሉትን ፕሬዚደንት ዩዌሪ ሙሴቬኒን በመቃወም፤ ቀዳሚ የሆነው የተቃዋሚ ፓርቲ መሪ ቦቢ ዋይን ዛሬ ማክሰኞ ዋና ከተማዋ ካምፓላ ሰሜናዊ ዳርቻ በደህንነት አባላት በተተኮሰ ጥይት እግሩን መመታቱን ፓርቲው አስታውቋል።
ከፖፕ ሙዚቃ ወደ ፖለቲካ ፊቱን ያዞረው እና በመድረክ ስሙ ቦቢ ዋይን የተባለው ሮበርት ኪያጉላኒ በጎርጎርሳዊያኑ 2021 ፕሬዚዳንታዊ ምርጫ ዩጋንዳን ለአራት አስርት ዓመታት ያህል የመሩትን ሙሴቬኒን በመከተል...