በማረቆ ልዩ ወረዳ እና የመስቃን ቤተ ጉራጌ ግጭቶች ሳቢያ የሰላማዊ ሰዎች ግድያ መቀጠሉ ተገለጸ
በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በምስራቅ ጉራጌ ዞን የምስራቅ መስቃን ወረዳ እና በማረቆ ልዩ ወረዳ መካከል በተቀሰቀሰው ግጭት ሳቢያ ካለፈው አርብ እስከ ትላንት በስቲያ እሁድ በነበረው ጊዜ ውስጥ 12 ሰዎች መገደላቸውን ቤተሰቦቻቸው እና ነዋሪዎች አስታወቁ::
የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳደር አቶ እንዳሻው ጣሰው በአከባቢዎቹ ላለው የፀጥታ ችግሮችና ሰላማዊ ሰዎች ጥቃት የወረዳዎቹ አመራሮች እጅ እንዳለበት ጠቅሰው የተጠረጠሩም እየታሠሩ መኾናቸውን...