ኢትዮጵያ በዐዲሱ የሶማሊያ የሰላም ተልዕኮ ውስጥ የመካተት ፍላጎት እንዳላት ገለጸች
ኢትዮጵያ፣ በዐዲሱ የሶማሊያ የሰላም ተልዕኮ ውስጥ በመካተት ሽብርተኝነትን የመዋጋትና የሶማሊያን መንግሥት የመርዳት ፍላጎት እንዳላት አስታውቃለች፡፡
የኢትዮጵያ ውጭ ጉዳይ ሚኒስትር አምባሳደር ታዬ አጽቀሥላሴ፣ ዛሬ ዐርብ፣ ነሐሴ 24 ቀን 2016 ዓ.ም. በሰጡት ጋዜጣዊ መግለጫ ላይ፣ የአገሪቱ የውጭ ጉዳይ ፖሊሲ፣ ከጎረቤት ሀገራት ጋራ ያላትን ግንኙነት ለማጠናከርና ዓለም አቀፍ አጋርነቶችን ለመፍጠር ያለመ ነው፤ ብለዋል።
የውጭ ጉዳይ ሚኒስትሩ ይህን የተናገሩት፣...