በምዕራብ ጎንደር ዞን ሁለት የስደተኛ መጠለያዎች መዘጋታቸውን ተመድ አስታወቀ
በዐማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የነበሩት የተባበሩት መንግሥታት ድርጅት የአውላላ እና የኩመር የስደተኛ መጠለያዎች መዘጋታቸውን፣ የድርጅቱ የስደተኞች ጉዳይ ከፍተኛ ኮሚሽነር በምኅጻሩ ዩ.ኤን.ኤች.ሲ.አር ለአሜሪካ ድምፅ አስታወቀ፡፡
ሁለቱም መጠለያዎች የጸጥታ ችግር እንደነበረባቸው፣ የስደተኞች ተቋሙ ሲገልጽ ቆይቷል፡፡
የሱዳንን ጦርነት ሸሽተው እየመጡ ያሉትን ስደተኞች ለማስጠለልም፣ ከኢትዮጵያ የስደተኞች እና ከስደት ተመላሾች አገልግሎት ጋራ በመተባበር፣...